loading
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ሲጀመር፤ ቅዳሜ እና እሁድ ደግሞ ቀጥለው ይካሄዳሉ

  የሳምንቱ መርሀግብር ጨዋታዎች ዛሬ በሲዳማ ቡና እና ስሑል ሽረ መካከል ተካሂዶ፤ ባለሜዳው ሲዳማ 3 ለ 2 አሸንፎ ሁለተኛ ደረጃን ከፋሲል ተረክቧል፡፡ አዲስ ግደይ በጨዋታ እና በፍፁም ቅጣት ሁለት እና ዳዊት ተፈራ የድል ግቦችን ሲያስቆጥሩ ፤ ሳሊፍ ፎፋና የሽረን ሁለት ግቦች ከመረብ አገናኝቷል፡፡    በነገው ዕለት ደግሞ አራት ያህል ግጥሚያዎች አዲስ አበባ እና ክልል ላይ […]

የስፔን ላሊጋ የ33ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ይጀመራሉ

  ዛሬ ምሽት 4፡00 ላይ ዲፖርቲቮ አላቬስ በሜዳው ሪያል ቫያዶሊድን ይገጥማል፡፡ በነገው ዕለት ደግሞ ምሽት 3፡ 45 ላይ ባርሴሎና በካምፕ ኑ ሪያል ሶሴዳድን ያስተናግዳል፡፡ የዲዬጎ ሲሞኔው አትሌቲኮ ዴ ማድሪድ ወደ ኤይባር ተጉዞ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ ሴልታ ቪጎ ከ ጂሮና እና ራዮ ቫዬካኖ ከሁሴካ በዕለቱ የሚደረጉ ሌሎች ግጥሚዎች ናቸው፡፡ የሳምንቱ ጨዋታዎች ዕሁድ ሲቀጥሉ ሪያል ማድሪድ በሳንቲያጎ ቤርናባው […]

በአፍሪካ ታዳጊዎች እና ወጣቶች ውድድር ላይ 4ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን አቀባበል እና ሽልማት ተበረከተለት

በኮትዲቯር አስተናጋጅነት ከሚያዝያ 8-12/2011 ዓ.ም በተከናወነው የአፍሪካ ከ – 18 እና ከ – 20 አመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በሁለቱም የእድሜ እርከኖች 82 አትሌቶችን ጨምሮ 111 ልኡካንን በመያዝ የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ስድስት ወርቅ ፤ አስር ብር እና አስራ አራት ነሀስ በማምጣት በድምሩ 30 ሜዳሊያዎችን በማሳካት ፤ ከዉድድሩ ተሳታፊ ሀገራት በአጠቃላይ ሜዳሊያ ብዛት 4ኛ ደረጃን በመያዝ […]