loading
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የጅማ ኢንደስትሪ ፓርክ ጎበኙ፡፡

ከጅማ ኢንደስትሪ ፓርክ በተጨማሪ ዱከም ኢንዱስትሪያል ፓርክን ጨምሮ በጅማና በቦንጋ የሚገኙ የጫካ ቡናዎችን ጎብኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከተባበሩት ዓረብ ኢሚሬቶች ከመጡ ባለሀብቶች ጋር መጎብኘታቸውን የጅማ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በጉብኝቱ ወቅትም ባለሀብቶቹ በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ የመሰማራት ፍላጎት ማሳየታቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። በ61 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር […]

የኢትዮጵያ የሃይማኖት አባቶች በሀገሪቱ የተከሰቱ ግጭቶች እና እየተባባሰ የመጣውን ስርዓት አልበኝነትን አጥብቀን እናወግዛለን አሉ፡፡

የሀይማኖት አባቶቹ ይህንን ያሉት የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነዉ፡፡ የሃይማኖት አባቶቹ በቅርቡ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጅጅጋ ከተማ የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የሰው ህይወት መጥፋቱ እና አብያተ ክርስቲያናት መቃጠል የትኛውንም ሃይማኖት የማይወክል ኢ ሰብዓዊ ድርጊት ነዉ ብለዋል፡፡ በተያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣው ስርዓት አልበኝነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹት የሃማኖት አባቶቹ […]

ኢትዮጵያ ከቱሪስቶች 3. 5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር አገኝች፡፡

የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት በ2010 ዓ.ም ኢትዮጵያን ከጎበኙ 934 ሺ ቱሪስቶች 3.5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከጎብኝዎች መካከል የቻይና ቱሪስቶች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ሲሆን፤ የእንግሊዝ እና የአሜሪካን ዜግነት ያላቸዉ ቱሪስቶችም በብዛት ሀገራችንን ጎብኝተዋል፡፡ ለገቢዉ መገኘት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ከባለድርሻ አካላትጋር ዘርፉን ለማሳደግ በጋራ መስራቱና የኢትዮጵያ […]

የቡሄ ባህል መሰረታዊ ይዘቱን መቀየሩ አሳስቦኛል አለ::

ይህንን ያለዉ የአዲስ አበባ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ነዉ፡፡ በባህል እና ቱሪዝም ቢሮ የጋራ ባህል እሴትዳይሬክተር አቶ አለማየው ጌታቸው የቡሄ ባህል መሰረታዊ ይዘት እየተቀየረ መምጣቱንና ስነቃሎቹም ላይ ጥናት ሊደረግ መሆኑን ለአርትስ ቲቪ ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ባህል እና ቱሪዝም ቡሄን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ምንም አይነት እንቅስቃሴ አለማደረጉን ገልፀው በመጪው ቡሄ ስነቃላዊ ጥናቶችን ለማድርግ በፌደራል ደረጃ መስሪያ ቤቱ […]

በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊገነባ ነው ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊገነባ መሆኑን አስታወቀ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ለፋና እንደተናገሩት ፥ አዲስ የሚገነባውን አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለማስጀመር እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው። አውሮፕላን ማረፊያውን ለመገንባት የሚያስፈልገውን የቦታ ጥያቄ ለመፍታት ከኦሮሚያ ክልል ጋር ምክክር እየተደረገ መሆኑን አቶ ተወልደ ተናግረዋል። ሊገነባ የታሰበው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ […]

ኢትዮጵያ የአጼ ቴዎድሮስን ሹርባ ከእንግሊዝ ለማስመለስ ጥያቄ አቀረበች፡፡

እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1868 መቅደላ ላይ በኢትዮጵያና በእንግሊዝ መካከል በተደረገው ጦርነት የእንግሊዝ ወታደሮች ከዘረፏቸው ቅርሶች መካከል የአጼ ቴዎድሮስ ሹርባ ይገኝበታል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የንጉሱ ጉንጉን ጸጉር ለንደን ውስጥ በናሽናል አርሚ ሙዚየም ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ባለፈው ሚያዚያ ወር የአትዮጵያ አምባሳደር ሙዚየሙን ከገጎበኙ በኋላ የይመለስን ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ ለጊዜው ለጎብኝዎች እይታ ከተቀመጠበት ቦታ ገለል ተደርጓል ሲል ዘ ጋርዲያን […]

በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች 29 ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የቻይና መንግስት የሰጠውን ነፃ የትምህርት እድል አገኙ፡፡

ዥንዋ እንደዘገበው ተማሪዎቹ በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞችን የሚከታተሉ ሲሆኑ ከ29 ተማሪዎች ውስጥ የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችም ይገኙበታል፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያዉያን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የሰጠው ነፃ እድል በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን ጠንካራ የዲፕሎማሲ፣ የባህል እና የምጣኔ ሃብት ትስስር ያመለክታል ብለዋል፡፡ በሃገሪቱ የወደፊት እጣ ፋንታ ላይም […]

በትግራይ ክልል በመኾኒ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 425 ተቀጣጣይ ፈንጅ ተያዘ።

ተቀጣጣይ ፈንጁ 75 ኪሎ ግራም ክብደት ሲኖረው መኾኒ ከተማ ልዩ ስሙ ገረብ አባ ሃጎስ በተባለ ስፍራ የተያዘ ነው ተብሏል። ፈንጁ ድልድይ ስር ተደብቆ ወደ መቐለ ከተማ ሊሻገር ሲል በህዝቡ ጥቆማ መያዙንም የትግራይ ክልል የህዝብና የመንግስት ግንኙነት ቢሮ አስታውቋል።ፋና እንደዘገበዉ

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ ይገኛሉ፡፡

የ2010 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ባለድሉ ጅማ አባጅፋር እ እንደ ኦኪኪ አፎላቢ እና መሰሎቹ ወደ ሌላ ክለብ ማምራታቸውን ተከትሎም የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት እስካሁን በአጠቃላይ 11 ያህል ተጫዋቾችን ማስፈረም ችሏል፡፡ በትላንትናው ዕለትም ከረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን የተሰናበቱት አሉላ ግርማ እና ዘሪሁን ታደለ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ ቡናው አስቻለው ግርማ ጅማ አባጅፋርን የተቀላቀሉ ተጫዋቾች ሁነዋል። ወደ ዋናው […]