loading
ማላዊ በቮሮናቫይረስ ሳቢያ ሁለት የካቢኔ ሚኒስትሮቿን ማጣቷ በሀገሪቱ ትልቅ ሀዘን ፈጥሯል፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 05፣ 2013 ማላዊ በቮሮናቫይረስ ሳቢያ ሁለት የካቢኔ ሚኒስትሮቿን ማጣቷ በሀገሪቱ ትልቅ ሀዘን ፈጥሯል፡፡ የማላዊ ፕሬዳንት ላዛረስ ቺኩየራ የሚንስትሮቹን ሞት አስመልክተው ባደረጉት ንግግር የማይሰላ ኪሳራ ደርሶብናል ካሉ በኋላ በሀገሪቱ የሶስት ቀን ሀዘን መታወጁን ይፋ አድርገዋል በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ በኋላ ህይዎታቸው ያለፈው የትራንስፖርት ሚስትሩ ሲዲክ ሚያ እና የአካባቢ አስተዳደር ሚንስትሩ ሊንግሰን ብሬካኒያማ ናቸው፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው […]

ዩዌሬ ሙሴቬኒ የምርጫው ቀን ከመድረሱ በፊት የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እንዲዘጉ አዘዙ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 05፣ 2013 ዩዌሬ ሙሴቬኒ የምርጫው ቀን ከመድረሱ በፊት የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እንዲዘጉ አዘዙ፡፡ ዩጋንዳ ጃኑዋሪ 14 ለምታካሂደው ምርጫ የተሳሳተ መረጃን በማሰራጨት ሁከት እንዲቀሰቀስ ያደርጋል በሚል ስጋት ከምርጫው ቀን አስቀድሞ ላሉት ሁለት ቀናት የበይነ መረብ አገልግሎት ዝግ ተደርጓል፡፡ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው የሀገሪቱ የኮምኒኬሽን ቁጥጥር ባለስልጣናትም የሙሴቬኒን ትእዛዝ ተቀብለው የበይነ መረብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን […]

ቱኒዚያዊያን በመንግስት ላይ የጀመሩት ተቃውሞ ከአራት ቀናት በላይ አስቆጥሯል::

አዲስ አበባ፣ጥር 12፣ 2013 ቱኒዚያዊያን በመንግስት ላይ የጀመሩት ተቃውሞ ከአራት ቀናት በላይ አስቆጥሯል:: ተቃዋሚዎቹ ጎዳናዎችን በመዝጋትና ቁሳቁሶችን በእሳት በማቀጣጠል ቁጣቸው በአደባባይ ሲያሰሙ ታይተዋል፡፡ የተቃውሟቸው መነሻ በሀገሪቱ የተንሰራፋው ድህነትና የስራ አጥነት መባባስ መሆኑን ለተቃውሞ በወጡበት ወቅት ገልፀዋል፡፡ አልጀዚራ በዘገባው እንዳስነበበው ሰልፈኞቹ የተለያዩ ሱቆችንና የንግድ ተቋማትን በመዝረፍ ተግባር ላይ መሰማራታቸውም ተሰምቷል፡፡ ይህን ተከትሎም የቱኒዚያው ፕሬዚዳንት ካይስ ሰይድ […]

ግብፅ በመላ ሀገሪቱ ጣለችውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአስራአምስተኛ ጊዜ አራዘመች::

አዲስ አበባ፣ጥር 16፣ 2013  ግብፅ በመላ ሀገሪቱ ጣለችውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአስራአምስተኛ ጊዜ አራዘመች:: በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ተግባዋ የሚሆነው የአስቸኳይ ጊዜ አቃጅ ዳግም የታደሰው በፓርላመው ውሳኔና በፕሬዚዳንት አብደልፈታህ አልሲሲ ይሁንታ ነው፡፡ ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው ግብፅ የመጀመሪያውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የጣለቸው እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2017 ነበር፡፡ በወቅቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተደነገገው የሽበርተኝነትን አደጋ ለመከላከል በሚል […]

የሊቢያ ተፋላሚ ኃይሎች ስምምነት

አዲስ አበባ፣ጥር 17፣ 2013  የሊቢያ ተፋላሚ ኃይሎች ቁልፍ የመንግስት ተቋማትን የሚመሩ እጩዎችን ለመምረጥ ተስማሙ ::የሁለቱም ወገኖች ተወካዮች ሞሮኮ ላይ ባደረጉት አዲስ ውይይት የእጩዎቹ የምልመላ ሂደት ከማክሰኞ ጀምሮ እንደሚከናወን አስታውቀዋል፡፡ ተፋላሚ ሃይሎቹ የደረሱበት ስምምነት በሀገሪቱ ለአስር ዓመታት የተካሄደውን የእርስ በርስ ጦርነት እንዲያበቃ ለማድረግ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑ ነው የተመገረለት፡፡ ሂደቱ እስከመጭው ፌብሩዋሪ 2 ቀን ድረስ የሚጠናቀቅ ሲሆን […]

የማዕከላዊ አፍሪካ ዜጎች ወደጎረቤት ዲሞክራቲክ ኮንጎ መጠለያ ፍለጋ እየተሰደዱ ነው ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 21፣ 2013 የማዕከላዊ አፍሪካ ዜጎች ወደጎረቤት ዲሞክራቲክ ኮንጎ መጠለያ ፍለጋ እየተሰደዱ ነው ተባለ፡፡ ስደተኞቹ ቀያቸውን ጥለው የሚሰደዱት በሀገሪቱ ነፍጥ አንግበው ከሚዋጉ ሚሊሻዎች ጥቃት ህይዎታቸውን ለማዳን ሲሉ ነው፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው በአሁኑ ወቅት ከማዕከላዊ አፍሪካ ወደ ጎረቤትረ ዲሞክራቲክ ኮንጎ የተሰደዱ 30 ሺህ ዜጎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖራሉ፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት […]

ሞቃዲሾ ውስጥ የደረሰ የቦንብ አደጋ የሞትና የአካል ጉዳት አድርሷል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ጥር 24፣ 2013 ሞቃዲሾ ውስጥ የደረሰ የቦንብ አደጋ የሞትና የአካል ጉዳት አድርሷል ተባለ:: አደጋው የተፈፀመው በማዕከላዊ ሞቃዲሾ በሚገኘው አፍሪክ ሆቴል ላይ ሲሆን ታጣቂዎች በአካባቢው ሁከት ከፈጠሩ በኋላ ፍንዳታው መከተሉን የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ በአደጋው ሳቢያ አንድ ጡረተኛ የጦር ጄኔራልን ጨምሮ አምስት ሰዎች ህይዎታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ 10 ሰዎች በአደጋው ምክንያት የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው አፍሪካ […]

በሱዳን በተለያዩ ከተሞች በኑሮ ውድነት ሳቢያ አዲስ ተቃውሞ መቀስሰቀሱ ተሰማ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 3፣ 2013 በሱዳን በተለያዩ ከተሞች በኑሮ ውድነት ሳቢያ አዲስ ተቃውሞ መቀስሰቀሱ ተሰማ:: ተቃውሞው የተቀሰቀሰው በዳርፉር ግዛት በሚገኙ ከተሞች ሲሆን በሰልፉ የተሳተፉት በአብዛኛው ወጣቶች መሆናቸው ነው የተገለፀው፡፡ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ በኑሮ ውድነት ሳቢያ ለርሃብ መጋለጣቸውን የሚገልፁ ጥያቄዎችን ይዘው ነው ጎዳና የወጡት፡፡ በደቡብ ዳርፉር ግዛት ዋና ከተማ ኒያላ ለተቃውሞ የወጡት ወጣቶች ሊበትኗቸው […]

ጊኒ የኢቦላ ቫይረስ በወረርሽኝ ደረጃ መከሰቱን ይፋ አደረገች።

አዲስ አበባ፣የካቲት 8፣ 2013 ጊኒ የኢቦላ ቫይረስ በወረርሽኝ ደረጃ መከሰቱን ይፋ አደረገች። በጊኒ ደቡብ ምስራቅ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ለህልፈት ከተዳረጉት ሰዎች ባሻገር አራት ሰዎች ደግሞ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ተነግሯል። በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ጎዋኬ በአንድ የቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተሳተፉ 7 ሰዎች የማስመለስ፣ የመድማት እና ማስቀመጥ  እንዳጋጠማቸው ተጠቁሟል። የኢቦላ ቫይረስ የተገኘባቸው እነዚህ ሰዎች አሁን ላይ […]

አልጄሪያዊያን የሂራክ አመፅ ንቅናቄ ብለው የሚጠሩትን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘከር አደባባይ ወጥተዋል፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 አልጄሪያዊያን የሂራክ አመፅ ንቅናቄ ብለው የሚጠሩትን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘከር አደባባይ ወጥተዋል፡፡ የሂራክ ንቅናቄ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣር በ2019 ፕሬዚዳንት አብደልአዚዝ ቡተፍሊካን ከስልጣን ያስወገዱበት የተቃውሞ ሰልፍ ነው፡፡ ሰልፈኞቹ የኮሮናቫይረስ ሳያስፈራቸውና በአደባባይ በሰባሰብን የሚከለክለውን ህግ ወደጎን በመተው ነው እለቱን እያሰቡ ሌላ ጥያቄ ያነሱበት፡፡ አልጄሪያዊያኑ ያኔ ባነሱት ተቃውሞ ለሁለት አስርት ዓመታት ሀገሪቱን የመሩት ቡተፍላካ ከስልጣን […]