loading
የሳይበር ጥቃቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይችላሉ -የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት

አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 25፣2014 በሕዳሴው ግድብ እና በከፍተኛ የፋይናንስ ተቋማት ላይ ያነጣጠሩ የሳይበር ጥቃቶች መክሸፋቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ገለጸ። የሀገሪቱን ሰላም እና ዕድገት በማይፈልጉ ሀገራት የሚደገፍ ድርጅት የሕዳሴው ግድብ ግንባታን ለማስተጓጎል በማቀድ ‘ብላክ ፒራሚድ ዎር’ በሚል ስያሜ የሳይበር ጦርነት መክፈቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ተናግረዋል። የፋይናንስ ተቋማት የሚጠቀሙባቸው እና እርስ […]

ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር ለመገናኘት መጠየቃቸው ተነገረ::

አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 25፣2014 ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር ለመገናኘት መጠየቃቸው ተነገረ:: የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማስቆም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመምከር በሞስኮለመገኘት ቢጠይቁም እስካሁን ምላሽ አላገኙም ተብሏል። ፖፕ ፍራንሲስ ለጣሊያኑ ኮሪየር ዴላ ሴራ ጋዜጣ እንደተናገሩት የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ኪሪል ጦርነቱ […]

ኑ የአቅመ ደካሞችን ቤት እንስራ-ጠቅላይ ሚስትር ዐቢይ አህመድ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በአዲስ አበባ የአቅመ ደካሞችን ቤት እድሳት እንጀምራለን አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህንን ያሉት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ላይ በተገኙበት ወቅት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ በአዲስ አበባ ለአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት የሚሆን የመደመር መንገድ መጽሐፍ ተሽጦ ካስገኘው ገንዘብ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን […]

ሰሜን ኮሪያ በአንድ ዓመት ውስጥ 14ኛውን የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2014 ሰሜን ኮሪያ በአንድ ዓመት ውስጥ 14ኛውን የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች፡፡ ፒዮንግያንግ የአሁኑን የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራውን ያደረገችው የኒውክሌር መርሃ ግብሯን በከፍተኛ ፍጥነት ለማሳደግ እየሰራች መሆኗን ይፋ ባደረገች በሳምንት ውስጥ ነው ተብሏል፡፡ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉር አቋራጭ ሚሳኤል ባስወነጨፈች በአንድ ወር ጊዜ ሌላ […]

ሦስተኛው ዙር የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባት ከግንቦት ወር መጨረሻ ሳምንት ጀምሮ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች መሰጠት ሊጀምር ነው፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2014 ሦስተኛው ዙር የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባት ከግንቦት ወር መጨረሻ ሳምንት ጀምሮ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች መሰጠት ሊጀምር ነው፡፡ በሶስተኛው ዙር የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ከ25 ሚሊዮን ዶዝ በላይ ለመከተብ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታው ዶክተር ደረጀ ድጉማ በተለይ ሁለተኛው ዙር የኮቪድ-19 ዘመቻ እንደ ሀገር በርካታ ጠንካራ […]

የግብፅ የፀጥታ ሃይሎችና የ”አይ ኤስ አይ ኤል” ግብግብ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2014 በሲናይ በርሃ ለተገደሉት የግብፅ ወታደሮች አይ ኤስ አይ ኤል ሃላፊነቱን እደሚወስድ ገለጸ፡፡ ቡድኑ ባለፈው ቅዳሜ እለት በሲናይ በርሃ 11 የግብፅ ወታደሮችን መግደሉንና መሳሪያቸውን መማረኩን ነው ይፋ ያደረገው፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ከስዊዝ ካናል በስተምስራቅ በምትገኘው ኢማኢሊያ ከተማ መሆኑን አልጀዚራ በዘገባው አስነብቧል፡፡ አይ ኤስ አይ ኤል በሲናይ ባህረ ገብ በኬላ ጥበቃ ላይ በነበሩ […]

የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ ለአሽከርካሪዎች የሰጠው ማስጠንቀቂያ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 የትራንስፖርት አገልግሎቱን በሚያስተጓጉሉ የህዝብ ትራንስፖርት ሰጪ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ አስጠነቀቀ::የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር እጸገነት አበበ ለኢቢሲ እንደገለጹት፣ ማንኛውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች፣ ሸገር የብዙሃን ትራንስፖርት ድጋፍ ሰጪዎችን ጨምሮ በተመደቡበት የስምሪት መስመር በመገኘት በተቀመጠው የታሪፍ መጠን ብቻ አገልግሎቱን መስጠት ይገባቸዋል፡፡ በጥናት መመለስ […]

አንዲት በጎ አድራጊ ግለሰብ ለዘውዲቱ ሆስፒታል ዘመናዊ የአምቡላንስ ድጋፍ አደረጉ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 አንዲት በጎ አድራጊ ግለሰብ ለዘውዲቱ ሆስፒታል ዘመናዊ የአምቡላንስ ድጋፍ አደረጉ፡፡ የዘውዲቱ ሆስፒታል ፋርማሲስት የሆኑት ወይዘሮ ሃና ልካስ ለሆስፒታሉ ያደረጉት የአምቡላንሶ ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ሲሆን፥ በተለይ በእርግዝና ላይ ያሉ እናቶች አስፈላጊውን የህክምና ድጋፍ እያገኙ ወደ ሆስፒታል እንዲደርሱ እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡ አምቡላንሱ ዘመናዊ የመተንፈሻ ቬንትሌተር የተገጠመለት ሲሆን፤በተለይ እናቶች […]

በደቡብ ሱዳን የኮሌራ በሽታ መከሰቱ በደቡብ ሱዳን በተከሰተው የኮሌራ በሽታ አንድ ሰው ሲሞት 31 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ታውቋል ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 በደቡብ ሱዳን የኮሌራ በሽታ መከሰቱ በደቡብ ሱዳን በተከሰተው የኮሌራ በሽታ አንድ ሰው ሲሞት 31 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ታውቋል ተባለ፡፡ የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ከ2017 ወዲህ በደቡብ ሱዳን የኮሌራ በሽታ ሲከሰት ይህ የመጀመሪያው ነው ተብሏል፡፡ በሽታው የተከሰተው በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ዩኒቲ ግዛት ሩቦንካ ካውንቲ ሲሆን በበሽታው […]

በኢትዮጵያ ፍትህ እንዲረጋገጥ ብዙ ስራዎች ይቀራሉ-ኢ.ሰ.መ.ኮ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ለሰብአዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ፡፡ ጥሪው የቀረበው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የ10 ወር የሥራ  ክንውን ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕ እና የዴሞክራሲ ጉዳዮች  ቋሚ  ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ኮሚሽኑ ባለፉት 10 ወራት ግጭት የተከሰተባቸው 65 ቦታዎችን መድረሱን፣ ባለፉት 3 ወራት ብቻ 450 ሺህ ስደተኞችን የሚያስጠልሉ አስር […]