loading
በዲሞክራቲክ ኮንጎ የጣሊያን አምባሳደር በጉዞ ላይ እያሉ በደረሰ የታጣቂዎች ጥቃት መገደላቸው ተሰማ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 16፣ 2013 በዲሞክራቲክ ኮንጎ የጣሊያን አምባሳደር በጉዞ ላይ እያሉ በደረሰ የታጣቂዎች ጥቃት መገደላቸው ተሰማ:: አምባሳደር ሉካ አታናሲዮ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተሸከርካሪ በሚጓዙበት ወቅት ነው ከግል ጠባቂያችው ጭምር ባልታወቁ ሰዎች በጥይት ተመትተው የተገደሉት፡፡ አምባሳደሩን እና አጃቢያቸውን ሲያጓጓዝ የነበረውና የሀገሬው ተወላጅ የሆነው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ድርጅት ሾፌርም በደረሰው ጥቃት ተገድሏል ነው የተባለው፡፡ የዓይን እማኞች እንደተናገሩት […]

የናይጄሪያ ታጣቂ ቡድኖች አግተዋቸው የነበሩት 53 ሰዎችን ለቀቁ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 16፣ 2013 የናይጄሪያ ታጣቂ ቡድኖች አግተዋቸው የነበሩት 53 ሰዎችን ለቀቁ:: የሀገሪቱ ባለስልጣናት በሰጡት ማረጋገጫ ኒጀር ውስጥ በታጣቂዎቹ በእገታ ስር ከነበሩ ሰዎች መካከል 20 ሴቶችንና 9 ህፃናትን ጨምሮ 53ቱም ተለቀዋል፡፡ ሰዎቹ በታጣቂዎቹ ታፍነው የተወሰዱት ባለፈው ሳምንት በአውቶቡስ በሚጓዙበት ወቅት እንደነበር ተነግሯል፡፡ የኒጄር መንግስት ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ ታጋቾቹ በተቻለ ፍጥነት እንዲለቀቁ አስፈላጊው ድርድር ተደርጓል […]

ዲሞክራቲክ ኮንጎ በሀገሯ የሚገኙ ዲፕሎማቶች ከመንግስ እውቅና ውጭ ከዋና ከተማዋ እንዳይወጡ ከለከለች፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 18፣ 2013 ዲሞክራቲክ ኮንጎ በሀገሯ የሚገኙ ዲፕሎማቶች ከመንግስ እውቅና ውጭ ከዋና ከተማዋ እንዳይወጡ ከለከለች፡፡ ሀገሪቱ በዲፕሎማቶች ላይ ይህን እገዳ የጣለችው ሰሞኑን ለጉብኝት ከከተማ ውጭ ሲጓዙ የነበሩት የጣሊያኑ አምባሳደር መገደላቸውን ተከትሎ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ማንኛውም የዲፕሎማቲክ ሚሽን አባላት ከዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ለመውጣት ሲፈልጉ ቀድመው ለመንግስት ማሳወቅ ይኖርባቸዋል፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው ፕሬዚዳንት ፊሊክስ ሺኬሴዲ ከዚህ […]

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በትራምፕ ዘመን የተጣለውን የግሪን ካርድ ክልከላ ህግ ሸረውታል::

አዲስ አበባ፣የካቲት 18፣ 2013 ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በትራምፕ ዘመን የተጣለውን የግሪን ካርድ ክልከላ ህግ ሸረውታል:: ትራምፕ 100 ሺህ 14 በሚል ድንጋጌ ያጸደቁት የቪዛ ክልከላ አዋጅ መነሻው የአሜሪካዊያንን የሥራ እድል ይጋፋል የሚል እንደሆነ ደጋግመው ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ሆኖም አዲሱ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ይህ አዋጅ አሜሪካን የሚጠቅም ሳይሆን የሚጎዳ ነው በማለት በፊርማቸው ሽረውታል፡፡ የባይደን አስተዳደር በዋናነት ህጉን የሻረበትን […]

ጂ አይ ዜድ እና ኦሬንጅ የኦሬንጅ በይነ መረብ ማዕከልን በኢትዮጵያ ከፈቱ፡፡

ጂ አይ ዜድ እና ኦሬንጅ የኦሬንጅ በይነ መረብ ማዕከልን በኢትዮጵያ ከፈቱ፡፡ ማዕከሉ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቃዊ አፍሪካ ሶስተኛውና ወጣቶችን በበይነ መረብ ቴክኖሎጂ ለማሠልጠንና የተሻለ የሥራ ዕድል እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ባለፈም ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር የዲጂታል ክህሎትን የሚያጎለብትና ለልዩ ልዩ ፈጠራዎች የሚያነሳሳ የኦሬንጅ ዲጂታል ማዕከል […]

በአፍሪካ ለኮቪድ-19 ታካሚዎች ከፍተኛ የመተንፈሻ መርጃ መሳሪያ እጥረት አለ ተባለ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 24፣ 2013 በአፍሪካ ለኮቪድ-19 ታካሚዎች ከፍተኛ የመተንፈሻ መርጃ መሳሪያ እጥረት አለ ተባለ:: የኮሮናቫይረስ በአፍሪካ አህጉር ከተከሰተ ጀምሮ መካለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት አቅምን ያገናዘበ አጋዥ የመተንፈሻ መሳሪያ እጥረት ትልቅ ፈተና መሆኑ ነው የሚነገረው፡፡ በአሁኑ ወቅት በታዳጊ ሀጋራት የሚገኙ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በየቀኑ የኦክስጅን ድጋፍ እንደሚፈልጉ አፍሪካ ኒውስ በዘገባው አስነብቧል፡፡ የኦክስጅን እጥረት በበርካታ […]

በናይጄሪያ በታጣቂዎች ታግተው የነበሩ ልጆች ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸው ተሰማ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 25፣ 2013 በናይጄሪያ በታጣቂዎች ታግተው የነበሩ ልጆች ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸው ተሰማ:: ባለፈው ዓርብ በሰሜን ናይጄሪያ በአዳሪ ትምህርት ቤት ውስጥ እንዳሉ በታጣቂዎች ታግተው ተወስደው የነበሩ 279 ልጃገረዶች በሰላም ከወላጆቻቸው ጋር መቀላቀላቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡ ልጃገረዶቹ ከአጋቾቻቸው እጅ ነፃ እዲወጡ የግዛቲቱ አስተዳዳሪዎች ሰፊ ድርድር አድርገው እንደነበር ነው የተነገረው፡፡ ታጋቾቹ ነፃ ከወጡ በኋላ የጤናቸው ሁኔታ በምርመራ […]

ስድስተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ፓርቲዎች ገለጹ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 25፣ 2013 ስድስተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ፓርቲዎች ገለጹ:: በጋምቤላ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች  ምርጫው ያለንዳች እንከን እንዲሳካ ሰላማዊና ዴሞክራሲዊ ፉክክር  ለማድረግ እየተዘጋጁ መሆናቸውን አመራሮቹ  ተናግረዋል። የብልጽግና ፓርቲ ጋምቤላ ክልል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ላክድር ላክባክ እንዳሉት ፤ ብልጽግና በክልሉ ከሚገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ካለፈው ዓመት ጀምሮ በትብብር እየሰራ […]

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰቡን ችግር ለመፍታት የጀመራቸውን ስራዎች እንዲያጠናክር አሳሰቡ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 26፣ 2013 ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰቡን ችግር ለመፍታት የጀመራቸውን ስራዎች እንዲያጠናክር አሳሰቡ:: ፕሬዚዳንቷ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲው 70ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ወቅት ነው። ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲው በአፍሪካ ቀዳሚ እንደመሆኑ ለአፍሪካዊያን ወንድምና እህቶች የትምህርት እድል በመስጠት ያበረከተው አስተዋጽኦ የሚዘነጋ አይደለም ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል በነበረበት […]

የሮማው ሊቀጳጳስ አባ ፍራንሲስ በኢራቅ የሚያደርጉት ጉብኝት የበርካቶችን ቀልብ ስቧል::

አዲስ አበባ፣የካቲት 26፣ 2013 የሮማው ሊቀጳጳስ አባ ፍራንሲስ በኢራቅ የሚያደርጉት ጉብኝት የበርካቶችን ቀልብ ስቧል:: ፖፕ ፍራንሲስ በኢራቅ ይፋዊ ጉብኝት ሲያደርጉ የመጀመሪያቸው ሲሆን የኮሮቫይረስ ከተከሰተ ወዲህ ዓለም አቀፍ ጉ ሲያደርጉም ቀዳሚው ነው ተብሏል፡፡ የፖፑ ጉብኝት በኢራቅ ለሚገኙ ክስርስቲያኖች ልዩ ሃይማኖታዊ ትርጉም ያለው ሲሆን በጥንታዊት ባቢሎን ዘመን ጀምሮ የነበረውን የባህልና የቋንቋ እሴቶች ትስስር ያጠናክራል ነው የተባለው፡፡ ሊቀጳጳሱ […]