loading
ኢዴፓ ከሰማያዊ ፓርቲ፣ ከአርበኞች ግንቦት 7 እና ለአንድነትና ለፍትህ ንቅናቄ ጋር ለመወሃድ ውሳኔ አሳለፈ

ኢዴፓ ከሰማያዊ ፓርቲ፣ ከአርበኞች ግንቦት 7 እና ለአንድነትና ለፍትህ ንቅናቄ ጋር ለመወሃድ ውሳኔ አሳለፈ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ሁለተኛ ልዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል። ፓርቲው ከጉባኤው በኋላ ከሰማያዊ ፓርቲ፣ ከአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለፍትህ ንቅናቄ ፣ ከመኢዴፓና ከሌሎች ፍላጎቱ ካላቸው ፓርቲዎች ጋር ለመዋሃድ ውሳኔ አሳልፏል። የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው […]

መንግስትና የጋምቤላና አፋር ነፃ አውጪ ንቅናቄዎች ታረቁ

መንግስትና የጋምቤላና አፋር ነፃ አውጪ ንቅናቄዎች ታረቁ የኢትዮጵያ መንግስት ከጋምቤላና ከአፋር ነፃ አውጪ ንቅናቄዎች ጋር የእርቅ ስምምነት መፈረሙ ተነገረ። ስምምነቱ የተፈረመው በአስመራ ከተማ ከሁለቱ ፓርቲዎች ጋር በተደረገ ውይይት ነው ተብሏል። ስምምነቱ የተፈረመው የአገር መከላከያ ሚኒስትሯ ኢንጅነር አይሻ መሀመድና የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ኡስማን መሀመድ ሁመዳ፣ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ፣ በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር […]

በምዕራብ ወለጋ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት አምስት ሰዎች ተገደሉ

በምዕራብ ወለጋ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት አምስት ሰዎች ተገደሉ በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ወረዳ ሁምነ ዋቀዮ ተብሎ የሚጠራው ቀበሌ ውስጥ   ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 5 ሰዎች ተገድለዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ሶስቱ የኢትዮጵያ ዜጎች ሲሆኑ፣ ሁለቱ ደግሞ የውጭ ዜጎች መሆናቸውን ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡