loading
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በያዝነው ወር መጨረሻ በቻይና ጉብኝት ያደርጋሉ::

በቆይታቸውም ከፈረንጆቹ መስከረም 3 እስከ 4 ድረስ በቤጂንግ በሚካሄደው በቻይና አፍሪካ ፎረም ላይ እንደሚሳተፉ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ አስታውቀዋል። ከፎረሙ ጎን ለጎንም ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪ ኪያንግ ጋር ተገናኝተው ይወያያሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው። እንደ ፅህፈት ቤት ሀላፊው ገለፃ ቻይና ቀዳሚዋ የኢትዮጵያ የንግድ አጋር እና የቀጥታ […]

አዲስ የተሾሙ የክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚዎች ዝርዝር ይፋ ሆነ፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደር የጀመረዉን የለዉጥ ጉዞ ለማፋጠን እስከ ክፍለ ከተማ መዋቅሩን በአዳዲስና ብቁ አመራሮች እያደራጀ ነዉ ። በዚህ መሠረት የክፍለከተሞቹ ምክርቤቶች ባካሄዱት አስቸኳይ ጉባኤ አዳዲስ ስራ አስፈፃሚዎችን ሹመት ማጽደቁን ከንቲባ ጽህፈት ቤት ገልጻል፡፡አራዳ ክፍለ ከተማ ወ/ሮ አበባ እሸቴ፣ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ ወ/ሮ ህይወት ጉግሳ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ልደታ ክፍለ ከተማ አቶ አለማው ማሙዪ […]

ከብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ ነሃሴ 17 እና 18 ቀን 2010 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በብአዴን 12ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ረቂቅ ሪፖርትና ለጉባዔው በሚቀርቡ ሌሎች ወቅታዊና መደበኛ ጉዳዮች ላይ ተወያቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ የብአዴን 12ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በህዝቡ ሁለንተናዊ ተሳትፎና ባለቤትነት በሀገር ደረጃና ብአዴን በሚመራው የአማራ ክልል የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ […]

የቀድሞ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር በአዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ፋና እንደዘገበዉ አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር በቁጥጥር ስር የዋሉት በዛሬው እለት አዲስ አበባ አትላስ አካባቢ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነው። የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ምክር ቤት በትናንትናው እለት ባካሄደው አስቸኳይ የአቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ያለመከሰስ መብት ማንሳቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ምክር ቤት ከአቶ አብዲ በተጨማሪ የ6 የምክር ቤት አባላትን ያለመከሰስ መብትን አንስቷል።      

ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ የ1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ተፈቅዶላታል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ እንዳሉት ድጋፉ በቀጥታ የሀገሪቱን በጀት የሚደግፍ ነው፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው የዓለም ባንክን ጨምሮ ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት  በ97 በኢትዮጵያ በተካሄደው ምርጫ የተከሰተውን ቀውስ ተከትሎ ለቀጥታ በጀት የሚውል የገንዘብ ድጋፍ አድርገው አያውቁም፡፡ ለገንዘቡ መገኘት አሁን በኢትዮጵያ የመጣው ለውጥ ዋኛው ምክንያት መሆኑንም ዶክተር አብይ ተናግረዋል፡፡ የዓለም ባንክ ግሩፕ ፕሬዝዳንት ጂም ያንግ ኪም በበኩላቸው […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር መጨረሻ ለይ ጀርመን ሊጓዙ ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ከጀርመኗ ቻንስለር መራሂተ መንግስት ወይዘሮ አንግላ መርከል ጋር በስልክ አውርተዋል፡፡ የጠቅለይ ሚንስቴር ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍፁም አረጋ በገፃቸው እንዳስነበቡት ቻንስለር መርከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባጭር ጊዜ እያካሄዱ ላሉት የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎች በተለይም ከኤርትራ ጋር ለተፈጠረው ሰላም አድናቆታቸውን በመግለጽ እንኳን ደስ ያለዎት ብለዋቸዋል፡፡ ቻንስለሯም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ጀርመን ተገኝተው […]

የመንግስት ባለስልጣናት ቪ8 ተሽከርካሪዎችን ከተማ ውስጥ እንዳይጠቀሙ የሚከለክለው መመሪያ በቀጣዩ ሳምንት ተግባራዊ መሆን ይጀምራል

  ኤፍ.ቢ.ሲ  እንደዘገበዉ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና የሌሎች ተቋማት ሀላፊዎች ቪ8 ተሽከርካሪዎችን ከተማ ውስጥ እንዳይጠቀሙ የሚከለክለው መመሪያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው። መመሪያው ባለስልጣናቱ እና የስራ ሀላፊዎቹ ከዚህ ቀደም በከተማ እንቅስቃሴ ወቅት ይጠቀሙባቸው የነበሩ ቪ8 ተሽከርካሪዎችን ለመስክ ስራ ብቻ እንዲጠቀሙ የሚደነግግ መሆኑንም የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ሐጂ ኢብሳ በሰጡት መግለጫ፥ […]

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር ወደ 30 ለማድረስ እየሰራሁ ነው አለ፡፡

በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር ስድስት ደርሷል፡፡ የፓርኮቹ መገንባት እና ስራ ላይ መዋል የኢንቨስትመንት ዘርፉን ውጤታማ እንደሚያደርግ እና አሁን ካሉት ስድስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደስራ የገቡ እና በቅርቡ ስራ የሚጀምሩ መኖራቸውን በኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ተካ ገብረ እየሱስ ተናግረዋል፡፡ የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጥቅምት 2011 ስራ የሚጀምር ሲሆን በቂሊንጦም የመድሃኒት ማምረቻ ኢንዱስተሪ ፓርክ ሊገነባ መሆኑን ሰምተናል፡፡ […]

አርቲስት እና አክቲቪስት ታማኝ በየነ በመጪው ቅዳሜ ጥዋት ወደ ኢትዮጵያ ይገባል፡፡

የአዲስ አበባ ብዙሃን መገናኛ እንደዘገበው የታማኝ በየነ ወደ ሀገሩ መመለስ ከግለሰብም በላይ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን እርሱን ለመቀበል የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ ገልጿል፡፡ አርቲስት ታማኝ በየነን ለመቀበል የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳለው ታማኝ በመጪው ቅዳሜ አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ይደረግለታል፡፡ በቦሌ ዓለም አቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ፣በብሄራዊ ትያትር ቤት እንዲሁም በሚሊኒየም አዳራሽ በሚኖሩ መርሃ ግብሮች […]