loading
ብ/ጀነራል አሳምነው ፅጌ እና ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ በላሊላ አሸንድዬ ካባ ተደረበላቸው።

አሸንድዬ፣አሸንዳ ፣ሶለል እና ሻደይ የዓለም ሀብት የሚሆኑት በባለቤትነት ስንጠብቃቸው ነው ብለዋል የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ፎዚያ አሚን። የአሸንድዬ የሴቶች በዓል “አሸንድዬ ለሰላምና አንድነት በፍቅር ለመደመር” በሚል መሪ ቃል በላሊበላ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው። በበዓሉ ላይ ብ/ጀነራል አሳምነው ፅጌ ወጣቶች ለሰላም ስሩ ሲሉ ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ ደግሞ ባህል የሚታወቀው አገር ሲኖር ነው ብለዋል ። አርትስ ቲቪ […]

ኢንጂነር ታከለ ኡማ በኮየ ፈጬ ሳይት የሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚገኙበትን ደረጃ ጎበኙ

በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የተመራውና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ ልኡካን በ11ኛው ዙር የተላለፉ የኮዬ ፈጬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችን አነጋግረዋል። ነዋሪዎች የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ባለማሟላቱ ቅሬታቸውን ገልጸውላቸዋል በተለይም የውሃ፣ የመብራት  እና የባለድርሻ አካላት በቅንጅት ተናበው አለመስራት በኑሮአቸው ላይ ተጽዕኖ እንደፈጠረ ነው የገለጹት፡፡ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለም የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች የህብረተሰቡን ቅሬታ ወስደው […]

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ ነው አለ፡፡

ተቋሙ ባለፉት አመታት ለፓርቲ የወገነ አሰራር መተግበሩና ከተሰጠው አገራዊ ተልእኮ ውጪ ዜጎችን የማፈን የማሰርና ኢሰብአዊ ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱ ተቋሙ እንዲፈራ አድርጎት ቆይቷል ተብሏል፡፡ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ጀነራል አደም መሀመድ ከኢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ከተቋሙ አሰራር ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም ተቋሙ የተቋቋመበትን አዋጅ ማሻሻልን ጨምሮ የሪፎርም ስራዎችን እያከናወነ ነው ፡፡ በተቋማዊ የሪፎርም ስራው […]

ባለፈው ሰኔ በአሶሳ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡

ያን ግዜ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ለድጋፍ አጽድቋል፡፡ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መንግስት በግጭቱ ምክንያት ህይወታቸው ላለፈ 16 ግለሰቦች ቤተሰብ ለእያንዳንዳቸው 30 ሺ ብር፣ በግጭቱ ምክንያት ከባድ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው 11 ግለሰቦች ለእያንዳንዳቸው 20ሺ ብር እንዲሁም በግጭቱ ምክንያት ቀላል ጉዳት ለደረሰባቸው 78 ግለሰቦች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው 10 ሺ ብር […]

በፍቅር እንደመር በይቅረታ እንሻገር በሚል መሪ ቃል ጳግሜ 5 ቀን የአዲሱን አመት መግቢያ በማስመልከት አዲስቷን ኢትዮጵያን ለመገንባት ቃል የመግባት ፕሮግራም በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡

የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳች ፅህፈት ቤት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሣሁ ጎርፌ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በዝግጅቱ አድስቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት የሚያስችለንን ቃል የምንገባበት ከመሆኑም በላይ በሁለም የህብረተሰብ ከፍል እና በመላው ሀገሪቱ የመነቃቃት ስሜት በሚፈጠርበት በመደመር ስሜት በውጭ ሀገር የሚኖሩትን ጨምሮ አዲሲቷ ኢትዮጵያ በጋራ የምንገነባበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በዝግጅቱ ከ 2 መቶ በላይ ኤርትራውያን ለመጋበዝ ከውጭ ጉዳይ ጋር በጋራ በመሆን […]

የአቃቂ ግድብ መሙላት አደጋ ስለሚያስከትል የማስተንፈስ ስራ አሁንም ይቀጥላል ተባለ፡፡

ይህንን ያለዉ የአዲስ አበባ ዉሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ነዉ፡፡ በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሄደት መሪ አቶ እስጢፋኖስ ብስራት ለአርትስ ቲቪ በትላንትናው ዕለት አቃቂ አካባቢ የደረሰውን የጎርፍ አደጋ ተከትሎ በተለያዩ ማህበራዊ ድረገፆች ላይ የአቃቂ ግድብ ሞልቶ ለማስተንፈስ በተደረገ ጥረት ውስጥ ቸግሩ እንደተከሰተ እና የሚመለከተውም አካል ማስጠንቀቄያ እንዳልተሰጠ ተደርጎ ሲነገር የነበረዉ ሀሰት ነዉ ብለዋል፡፡፡ በክረምት ሁሌ የማስተንፈስ ስራ […]

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ብአዴን ወደፊት የሚመራባቸውን የፖለቲካ መስመሮች ለመወሰን እየመከረ ነው፡፡ 

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ይመራበት የነበረውን አብዮታዊ ዲሞክራሲ እናሻሽል ወይም አናሻሸል በሚሉ እና ሌሎች መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እየመከረ ነው፡፡ በዋናነትም አብዮታዊ ዴሞክራሲን እናሻሽል ወይም አናሻሸል? በሚል መሰረታዊ የማሻሻያ ጉዳዮችይወያያል፡፡ የድርጅቱ ስያሜ እና ዓርማ የአማራን ህዝብ አይወክልም በመባሉም ይመከርበታል፡፡ ድርጅቱ ባለፉት ጊዜያት ይመራባቸው የነበሩ ህጎች አንዳንዶቹ ወቅቱን ያላገናዘቡ በመሆኑ ይመከርባቸዋል፡ የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ በክልሉ ካሉ አመራሮች የሰበሰባቸውን […]

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል 11 ዞኖች ከተውጣጡ የሴቶችና ወጣቶች ተወካዮች፣ ምሁራንና ከተለያዩ የአለም አገራት ከመጡ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በክልሉ ወቅታዊና የለውጥ እንቅስቃሴዎች ላይ እየተወያዩ ነው።

  ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል 11 ዞኖች ከተውጣጡ የሴቶችና ወጣቶች ተወካዮች፣ ምሁራንና ከተለያዩ የአለም አገራት ከመጡ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በክልሉ ወቅታዊና የለውጥ እንቅስቃሴዎች ላይ እየተወያዩ ነው። ምንጭ ኢቢሲ  

በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ አድናቆት አለን አሉ ኮንግረስማን ክሪስ ስሚዝ፡፡

  አርትስ 18/12/2010 የአሜሪካ ኮንግረንስ አባላት ልኡካን ቡድን ከኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይቷል፡፡ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ ገጹ እንዳስታወቀዉ ኮንግረንስማን ክሪስ ስሚዝ አሁን እየተካሄደ ያለው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጠል ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ዕድገት ለምታደርገው አስተዋጽኦ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀው […]