loading
በሪል ስቴት ኩባንያዎች ላይ የተጣለው ዕግድ እንዲነሳ መመርያ ተሰጠ

በሪል ስቴት ኩባንያዎች ላይ የተጣለው ዕግድ እንዲነሳ መመርያ ተሰጠ

የመሬት ቢሮ ያቆመውን አገልግሎት በድጋሚ መስጠት ጀመሯል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ለሪል ስቴት ኩባንያዎች መስጠት አቁሞ የነበረውን አገልግሎት በድጋሚ መስጠት እንዲጀምር መመርያ ሰጡ፡፡

ፍርድ ቤት እንጂ የፌዴራል ፖሊስ የማገድ ሥልጣን ስለሌለው፣ የሪል ስቴት ኩባንያዎች ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ተደርጓል፡፡

በሪል ስቴት ልማት ዘርፍ የተከሰተውን ችግር ለመፍታት ምክትል ከንቲባው ከሪል ስቴት ኩባንያዎች ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በዉይታቸዉም ከአንድ ወር በፊት የፌዴራል ፖሊስ፣ በወንጀል የጠራጠራቸውን 28 የሪል ስቴት ኩባንያዎች እንዲታገዱ ለክፍለ ከተሞች ደብዳቤ በመጻፉ የተፈጠረው ችግር ነው፡፡ ከተዘረዘሩት 28 ሪል ስቴት ኩባንያዎች መካከል፣ በሪል ስቴት ልማት ምንም ተሳትፎ እንደሌላቸው የገለጹና በዝርዝሩ ውስጥ በመካተታቸው ብቻ ሌሎች ሥራዎቻቸው ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩ እንዲስተካከል የጠየቁም አሉ፡፡

ምክትል ከንቲባው በሰጡት መመርያ በሪል ስቴት ልማት ዘርፍ በአስተዳደሩና በግል ተዋናዮች በኩል ያሉ ችግሮችን ለይቶ፣ በግንባታ ቦታ ላይ ተገኝቶ ችግሩን የመፍታት ሥልጣን የተሰጠው ግብረ ኃይል ተቋቁሟል፡፡

ግብረ ኃይሉ በመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የሚመራ ነው፡፡ ከፕላን ኮሚሽን፣ ከኮንስትራክሽን ቢሮ፣ ከገቢዎች ቢሮ፣ ከግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣንና ከከንቲባ ጽሕፈት ቤት የተውጣጡ አባላት ይኖሩታል፡፡

ሪፖርተር እንደዘገበዉ ከዚህ በተጨማሪ ከሪል ስቴት ኩባንያዎች በተለይም ፀሐይ ሪል ስቴትና ሰንሻይን ሪል ስቴት የተካተቱ ሲሆን፣ ግብረ ኃይሉ የሚያካሂደውን ሥራ ምክትል ከንቲባው በቀጥታ እንደሚከታተሉ ታውቋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *