loading
ከ4 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው 6 መቶ 38 ሳጥን ቢራን ከጫኑት ተሽከርካሪዎች ጋር ሰርቀው ሊሰወሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 14፣2013  ከ4 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው 6 መቶ 38 ሳጥን ቢራን ከጫኑት ተሽከርካሪዎች ጋር ሰርቀው ሊሰወሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን የፈፀሙት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አዲሱ ሚካኤል ገነት ህንፃ ተብሎ በሚጠራው የቢጂ. አይ ኢትዮጵያ ምርቶች ወኪል አከፋፋይ አልታድ ኢትዮጵያ […]

ወርቅን በብር ቀይሮ ለማስቀመጥ በሚሰሩ አሻጥሮች አብዛኛው የወርቅ ምርት ባንክ እየገባ አደለም ተባለ።

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 17፣2013  ወርቅን በብር ቀይሮ ለማስቀመጥ በሚሰሩ አሻጥሮች አብዛኛው የወርቅ ምርት ባንክ እየገባ አደለም ተባለ። የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ይህንን ያሉት ከጋምቤላ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር የማዕድን ዘርፉ በሚጠናከርበት ዙሪያ በተወያዩበት ወቅት ነው። ፈቃድ በተሰጣቸው የወርቅ አዘዋዋሪዎች አስፈላጊውን ክትትልና ጥናት በማካሄድ እርምጃ መውስድ እንሚያስፈልግም ነው የገለጹት። በጋምቤላ ክልል […]

የዲግሪ ተመራቂው ወጣት ቅድሚያ ለሀገር ህልውና ብሎ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ገባ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 18፣2013 በተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ትምህርት በዲግሪ የተመረቀው ወጣት ስራ ቢያገኝም ቅድሚያ ለሀገር ብሎ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ገባ፡፡ ከአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ወታደራዊ ስልጠናውን የተቀላቀለው ወጣት በተፈጥሮ ሀብት አያያዝ የትምህርት ዘርፍ የድግሪ ምሩቅ ሲሆን ስራ ቢያገኝም ቅድሚያ ለሀገሬ ህልውና ብሎ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ገብቶ እየሰለጠነ ይገኛል፡፡ የዲግሪ ተመራቂው ነጋ ምህረት ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ […]

በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ 1ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የኮቪድ-19 ክትባት ለመከተብ ዘመቻ ተጀመረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 18፣2013  በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ 1ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎችን ለመከተብ ዘመቻ መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ አስታወቁ፡፡ በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ የሚገኘውን የኮቪድ -19 ስርጭት በርብርብ መግታት ካልተቻለ ዋጋ ሊያስከፍል እንደሚችል ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ዶክተር ዮሐንስ እንደገለጹት ባለፉት አራት ሳምንታት በኮቪድ -19 የመያዝ ምጣኔው፣ በጽኑ የሚታመሙ ሰዎች ቁጥር እና […]

በትግራይ ክልል ያለው ችግር የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ነው – የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 18፣2013  በትግራይ ክልል ያለው ችግር የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ በመሆኑ መንግሥታቸው ጣልቃ የመግባት አጀንዳን እንደማይደግፍ የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት ገለጹ፡፡ በደበብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንትና የአገልግሎት ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ ከሆኑት ሁሴን አብዱል ባጊ አኮል ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ መክረዋል። አምባሳደር ነቢል የሁለቱ […]

ሶስተኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን የሚያሳይ ምልክት መታየቱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ።

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 18፣2013 ሶስተኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን የሚያሳይ ምልክት መታየቱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ። ዶክተር ሊያ ጉዳዩን አስመልክተው ዛሬ በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 5 ሺህ 547 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡ በአንድ ቀን ውስጥ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች መያዛቸውን የገለጹት ሚኒስትሯ የወረርሽኙ መጠን ከዚህ በፊት ካለው በእጅጉ መጨመሩን […]

በአሜሪካ ሕፃናት በዴልታ ኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ በአሜሪካ ሕፃናት በኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ ተጠቆመ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 18፣2013 በአሜሪካ ሕፃናት በዴልታ ኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ በአሜሪካ ሕፃናት በኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ የአሜሪካ ፔዲያትሪክስ አካዳሚ እና የሕፃናት ሆስፒታል ማሕበር ባወጡት ሪፖርት÷ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ በሀገሪቱ ወደ 94 ሺህ የሚጠጉ ሕፃናት በቫይረሱ ተጠቅተዋል ፡፡ ሉዚያና እና ፍሎሪዳ በርካታ በኮቪድ 19 ቫይረስ የተጠቁ ሕፃናት ሪፖርት የተደረገባቸው አካባቢዎች እንደሆኑም ተመላክቷል፡፡ […]

የደቡብ ዕዝ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የዕዙ የሰራዊት አባላት ሆነው ለአሸባሪው ህወሓት ሲሰሩ በነበሩ የሰራዊት አባላት ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 19፣2013 የደቡብ ዕዝ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የዕዙ የሰራዊት አባላት ሆነው ለአሸባሪው ህወሓት ሲሰሩ በነበሩ የሰራዊት አባላት ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ የሰራዊት አባላቱ ለህገ-መንግስቱና ለሀገራቸው የገቡትን ቃል ኪዳን ወደጎን በመተው የሰራዊቱን አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች አደጋ ላይ የሚጥሉና የትግራይ ልዩ ሃይልን የሚያጠናክሩ ተግባራትን ሲያከናውኑ መቆየታቸው በችሎቱ ተነስቷል፡፡ በተለይም የሰራዊቱን ልዩ ልዩ ምስጢራዊ ሰነዶች ለትግራይ ልዩ […]

ህገወጥ ነጋዴዎችን በአከባቢያችሁ ለሚገኝ ፖሊስ ጠቁሙ

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 19፣2013  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ለንግድ ማህበረሰቡ ማሳሰቢያ ሰጠ፡፡ ቢሮው አንዳንድ ስግብግብ ነጋዴዎች ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ በአቋራጭ ለመክበር እና ሆን ብሎ ህገ-ወጥ የዋጋ ጭምሪ እና ኢኮኖሚያዊ አሻጥር ለመፍጠር ጥረት ማድረግ ላይ መሆናቸውን ድርሼበታለሁ ብሏል፡፡ ስለሆነም በማንኛውም ንግድ ስራ ላይ ተሰማርታችሁ የምትገኙ ነጋዴዎች ለሽያጭ በሚቀርቡ ማለትም በተለይ ከውጪ ሃገር […]

የኢትዮጵያ ሽልማት በኢትዮጵያ ሊካሄድ ነው፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 19፣2013  በዓለም ፀሐይ ወዳጆ የጥበብ መድረክ አዘጋጅነት ከዚህ በፊት በአሜሪካ ለሶስት ዙር የተካሄደው የኢትዮጵያ ሽልማት ለአራተኛ ግዜ በኢትዮጵያ ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ፡፡ በጥር 2011 ዓ.ም በሰሜን አሜሪካ ኮሎራዶ የተቋቋመው ዓለም ፀሐይ ወዳጆ የጥበብ መድረክ ለመጀመርያ ጊዜ በሀገራችን ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ሄልተን ነሀሴ 29፣ 2013 ዓ.ም በዕለተ ቅዳሜ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ታዉቋል፡፡ […]