loading
የትምህርት ሚኒስቴር የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሀ-ግብር በይፋ ተጀመረ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29፣ 2013 የትምህርት ሚኒስቴር የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሀ-ግብር በይፋ ተጀመረ:: የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የአቅመ ደካሞችን ቤቶች በማደስ በትምህርት ዘርፉ የሚካሄደውን የክረምት የበጎ አድራጎት መርሀ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በበጎ አድራጎት መርሀ ግብሩም በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በክፍለ ከተማው 15 የአቅመ ደካሞች ቤት እንደሚታደስም ተገልጿል። የትምህርት […]

ካይሮ የግድቡ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት መጀመሩን የሚገልፅ ደብዳቤ ከአዲስ አበባ ደርሶኛል አለች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29፣ 2013 ካይሮ የግድቡ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት መጀመሩን የሚገልፅ ደብዳቤ ከአዲስ አበባ ደርሶኛል አለች፡፡ የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር ሞሀመድ አብደል አቲ የኢትዮጵያው የውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስትር ኢንጂኔር ስለሺ በቀለ በላኩልኝ ይፋዊ ደብዳቤ ሀገራቸው በተናጠል ውሳኔዋ ፀንታ ሁለተኛውን ዙር ሙሌት መጀመሯን አረጋግጠውልኛል ብለዋል፡፡ አብደል አቲ ለኢንጂኔር ስለሺ በጻፉት የመልስ ደብዳቤ ግብፅ የኢትዮጵያን […]

የክብርት ዶክተር አበበች ጎበና የቀብር ስነ-ስርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29፣ 2013 በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ፓትርያሪክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ፣ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተዋል፡፡ አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና ከሀገር ባለውለታነት አልፈው ለሰው ልጆች ትልቅ […]

የፀጥታው ምክር ቤት በህዳሴው ግድብ ውሳኔ የመስጠት ኃላፊነት የለውም-የናይል ተፋሰስ ሀገራት

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 1፣ 2013  የፀጥታው ምክር ቤት በህዳሴው ግድብ ውሳኔ የመስጠት ኃላፊነት የለውም-የናይል ተፋሰስ ሀገራት የናይል ተፋሰስ ሀገራት በአፍሪካ ህብረት አስተባባሪነት የሚደረገው የግድቡ ድርድር ሂደት ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት ትክከለኛው መንገድ መሆኑን ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ድርድሩ ያለበትን ደረጃ በሚመለከት በኢትዮጵያ ለሚገኙ የተፋሰሱ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ገለፃ አድርገዋል፡፡ […]

ዙማ ከፖሊስ ጋር ድብብቆሽ በቃኝ አሉ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 1፣ 2013 የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮቭ ዙማ ለፖሊስ እጃቸውን መስጠታቸው ተሰማ፡፡ የተመሰረተባቸውን የሙስና ክስ ችሎት ቀርበው እንዲያስረዱ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት የሰጠውን ትዕዛዝ ባለማክበር የ15 ወራት እስር የተፈረደባቸው ዙማ ቅጣቱ እንዲቀርላቸው አቤት ብለው ነበር፡፡ የተወሰነባቸውን ቅጣት እንዲፈፅሙ ሲጠየቁ አሻፈረኝ ብለው የነበሩት ፕሬዚዳንቱ ፖሊስ በሃይል ይዞ ወደ አስር ቤት ሊወስዳቸው በሚዘጋጅበት በገዛ […]

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ በሳምንታዊ መግለጫቸው በአበይት ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና የዜጋ ዲፕሎማሲ ክንውኖችን ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 2፣ 2013  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ በሳምንታዊ መግለጫቸው በአበይት ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና የዜጋ ዲፕሎማሲ ክንውኖችን ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡ ትናንት በመንግሥታቱ የድርጅት ፀጥታ ምክር ቤት የቀረበው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ የሶስትዮሽ ድርድሩ ወደ አፍሪካ ህብረት እንዲመለስ የሚል ሀሳብ መቅረቡ ትልቅ ዲፕሎማሲ ስኬት ነው ብለዋል። ቋሚ አባላትም ሁሉም በሚባል […]

ልጆቿን የምታስርብ ሃገር ልትለማ አትችልም-ወይዘሮ ፍሬዓለም ሽባባው

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 2፣ 2013 በህፃናት ምገባ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ስኩል ሚል ኢኒሸቲቭ የተማሪዎችን የምግብ እጥረት ለመቅረፍ የድርሻችንን እንወጣ ሲል ጥሪ አቀረበ፡፡ ድርጅቱ ይህን ያለው በተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም የተሰሩትን ሥራዎች ማሳያና የምስጋና መርሐ ግብር ባካሄደበት ወቅት ነው። የስኩል ሚል ኢኒሸቲቭ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍሬዓለም ሽባባው ሃገር የምትለማው ዜጎቿን ስትንከባከብ ነው ብለዋል። ልጆች ባሉበት ሁሉ […]

ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ግልፅ መርህ አስቀምጣ እየተጓዘች ነው-ኢንጅኔር ስለሺ በቀለ

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ግልፅ መርህ አስቀምጣ እየተጓዘች ነው-ኢንጅኔር ስለሺ በቀለ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ማብራርያ ሰጡ፡፡ ሚኒስትሩ ለዋና ጸሐፊው ግንባታው ስላለበት ሁኔታ፣ ስለሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ስለሚካሄደው ድርድር ተገቢውን ማብራሪያ ሰጥተዋል ። […]

የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባለ ስልጣናት ግድያ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የመከላከያ ምስክሮችን መስማት ጀመረ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013   የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባለ ስልጣናት ግድያ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የመከላከያ ምስክሮችን መስማት ጀመረ፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በአማራ ክልል ባለስልጣናት ግድያ እጃቸው አለበት በተባሉት በእነሻምበል መማር ጌትነት መዝገብ የተከሰሱ 32 ተከሳሾችን የመከላከያ ምስክሮች ነው ማዳመጥ የጀመረው፡፡ በዚሁ የክስ መዝገብ ጉዳያቸው ሲታይ ከነበሩት 55 ተከሳሾች […]

ግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ህብረት አባላት ላይ የዕድሜ ልክ እስራ  ውሳኔ አስተላለፈች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ህብረት አባላት ላይ የዕድሜ ልክ እስራ  ውሳኔ አስተላለፈች፡፡ የሀገሪቱ ከፍተኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት የፖሊስ አባላትን በመግደልና እስር ቤት ሰብረው እስረኞችን በማስመለጥ ወንጀል በተከሰሱ የህብረቱን መሪ ሞሐመድ ባዴን ጨምሮ በ10 ግለሰቦች ላይ ነው ወሳኔውን ያሳለፈው፡፡ ተከሳሾቹ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር በ2011 በግብፅ በተቀሰቀሰው አብዮት 20 ሺህ የሚሆኑ እስርኞችን እንዲያመልጡ […]