loading
የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱ የኮሮናቫይረስ ዝርያ ባለፈው ሳምንት በ16 በመቶ ቀንሶ መታየቱን ገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱ የኮሮናቫይረስ ዝርያ ባለፈው ሳምንት በ16 በመቶ ቀንሶ መታየቱን ገለፀ፡፡ ድርጅቱ ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ባወጣው ሪፖርት ከኮቪድ 19 ጋር የተያያዘ የሞት መጠን መቀነሱንም አስታውሷል፡፡ ድርጅቱ ከስድስት የቁጥጥር ቀጠናዎች ከተላኩለት የበሽታው ስርጭት ሪፖርቶች መካከል በአምስቱ አዲሱ ቫይረስ በሁለት አሃዝ መቀነስ ሲያሳይ በሜዲትራኒያን አካባቢ ብቻ በ7 በመቶ ጭማሪ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ […]

ኢዜማ መንግስት የፓረቲያቸዉን አባል ሕይወት የቀጠፉትን ወንጀለኞች አድኖ ሕግ ፉት ባስቸኳይ እንዲያቀርብ ጠየቀ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 ኢዜማ መንግስት የፓረቲያቸዉን አባል ሕይወት የቀጠፉትን ወንጀለኞች አድኖ ሕግ ፉት ባስቸኳይ እንዲያቀርብ ጠየቀ፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ የፓርቲዉ አባል አቶ ግርማ ግድያን ተከትሎ በሰጠዉ መግለጫ ፤ ከዚህ በፊት በቢሾፍቱ ከተማ የምናደርገዉ እንቅስቃሴ ላይ የተለያዩ ችግሮች ሲያጋጥሙ እና አባላቶቻችን ላይ ማዋከብ ሲያገጥመን የቆየ ነዉ ብሏል፡፡ የምርጫ ወረዳ መዋቅራችን የሚጠቀምበት ጽ/ቤት ለመክፍት […]

አልጄሪያዊያን የሂራክ አመፅ ንቅናቄ ብለው የሚጠሩትን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘከር አደባባይ ወጥተዋል፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 አልጄሪያዊያን የሂራክ አመፅ ንቅናቄ ብለው የሚጠሩትን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘከር አደባባይ ወጥተዋል፡፡ የሂራክ ንቅናቄ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣር በ2019 ፕሬዚዳንት አብደልአዚዝ ቡተፍሊካን ከስልጣን ያስወገዱበት የተቃውሞ ሰልፍ ነው፡፡ ሰልፈኞቹ የኮሮናቫይረስ ሳያስፈራቸውና በአደባባይ በሰባሰብን የሚከለክለውን ህግ ወደጎን በመተው ነው እለቱን እያሰቡ ሌላ ጥያቄ ያነሱበት፡፡ አልጄሪያዊያኑ ያኔ ባነሱት ተቃውሞ ለሁለት አስርት ዓመታት ሀገሪቱን የመሩት ቡተፍላካ ከስልጣን […]