loading
የቀድሞው የማሊ ፕሬዚዳንት ቡበከር ኬታ ታው ሆስፒታል ገብተዋል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012  የቀድሞው የማሊ ፕሬዚዳንት ቡበከር ኬታ ታው ሆስፒታል ገብተዋል ተባለ:: በመፈንቅለ መንግስት መካሄዱን ተከትሎ ለ10 ቀናት በወታደራዊ ጁንታው ቁጥጥር ስር የነበሩት ኢብራሂም ቡበከር ኬታ በተለቀቁ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው ሀኪም ቤት የገቡት፡፡ አሶሼትድ ፕሬስ በዘገባው እንዳስነበበው የፕሬዚዳንቱ የጤና ሁኔታ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ እስካሁን የተብራራ መረጃ የለም፡፡ ኤን 5 የተሰኘው የሀገሪቱ ተቃዋሚ […]

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ህግ ለማያከብሩ ከተሞች ከፌደራል የሚመደብላቸውን ፈንድ እንደሚያቋርጡ አሰጠነቀቁ::

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012 ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ህግ ለማያከብሩ ከተሞች ከፌደራል የሚመደብላቸውን ፈንድ እንደሚያቋርጡ አሰጠነቀቁ:: ፕሬዚዳንቱ ሲያትል ፣ ፖርትላንድ ፣ ኒው ዮርክ እና ዋሽንግተን ከተሞችን በስም ጠቅሰው ህግ የማያከብሩ ከሆነ ከፌደራል የሚደረግላቸው የገንዘብ ድጋፍን እንደሚቆም የሚያስገነዝብ የውስጥ ማስታወሻ መፈረማቸው ተሰምቷል፡፡ በኔ አስተዳደር ከግብር ከፋዮች የሚሰበሰብ ዶላር ህገ ወጥ ትን ለማጠናከር አይባክንም ያሉት ትራምፕ እነዚህን ከተሞች […]

የአንድ ሀገር ብልጽግና ከማኅበራዊ ኃላፊነት መጎልበት ጋር ከፍተኛ ትሥሥር አለው ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ ገለፁ:

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012 የአንድ ሀገር ብልጽግና ከማኅበራዊ ኃላፊነት መጎልበት ጋር ከፍተኛ ትሥሥር አለው ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ ገለፁ::የአንድ ሀገር ብልጽግና ከማኅበራዊ ኃላፊነት መጎልበት ጋር ከፍተኛ ትሥሥር እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት “ማኅበራዊ ኃላፊነት ዝቅተኛ የሆነባቸው ሀገራት ለዕድገት ብዙ ማገዶ ይጨርሳሉ” ብለዋል። “የመሠልጠን ጉዟቸውም መሰናክል […]

የአፋር ክልል አሚበራ ወረዳ ከትናንት ሌሊት ጀምሮ የተከሰተው ጎርፍ

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012 በአፋር ክልል አሚበራ ወረዳ ከትናንት ሌሊት ጀምሮ የተከሰተው ጎርፍ ተከትሉ በውሃ የተከበቡ ሰዎችን ለማውጣት በሄሊኮፕተር የታገዘ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች ቀደም ሲልም ተከስቶ በነበረው ጎርፍ የተጉዱ ወገኖች ለመደገፍ ሲሰራ ቆይቷል። በጽህፈት ቤቱ የቅድመ-ማስጠንቀቂያና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ አይዳሂስ ያሲን እንደገለጹት በክልሉ […]

አቶ ልደቱ አያለው በምስራቅ ሸዋ ዞን ቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በሌላ መዝገብ ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012 አቶ ልደቱ አያለው በምስራቅ ሸዋ ዞን ቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በሌላ መዝገብ ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። አቃቤ ህግም በችሎቱ ተገኝቶ እጃቸው ላይ የተገኘ የሽግግር መንግስት መመስረቻ ሰነድ የሚል እና ለውጡን ተቃርኖ “ለውጡ ከድጡ ወደ ማጡ” የሚል ርእስ የተሰጠው የፖለቲካ ይዘት ያለውና ህገ መንግስቱን ለመናድ አልሞ የተዘጋጀ ሰነዶችን ተከትሎ ክስ ለመመስረት እየመረመረ […]

የአሜሪካ ልማት ተርአዶ ድርጅት የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ለኢትዮጵያ አበረከተ::

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012 የአሜሪካ ልማት ተርአዶ ድርጅት የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ለኢትዮጵያ አበረከተ:: ዓለም አቀፉ የአሜሪካ ልማት ተርአዶ ድርጅት (ዩ.ኤስ.ኤይድ) የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ለኢትዮጵያ አበረከተ። ዩ.ኤስ.ኤይድ ኢትዮጵያ በትዊተር ገፁ እንዳስታወቀው፥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ ባለበት በዚህ ወቅት ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ጋር በመተባበር የመመርመር አቅመን ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ […]

የጎንደር ከተማን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሻሻል በ64 ሚሊዮን ብር የተቆፈሩ::

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 28፣ 2012 የጎንደር ከተማን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሻሻል በ64 ሚሊዮን ብር የተቆፈሩ:: ጥልቅ ጉድጓዶች በቅርቡ አገልግሎት እንደሚጀምሩ የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።   የአስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሃይማኖት በለጠ ለኢዜአ እንደገለጹት የከተማውን የውሀ አቅርቦት ለማሻሻል በመካከለኛ ጊዜ እቅድ ከተያዙ አምስት ጥልቅ ጉድጓዶች የሁለቱ ቁፋሮ ተጠናቋል ። ጥልቅ ጉድጓዶቹ የሚያመነጩትን ውሀ ወደ […]