loading
መከላከያ ሰራዊት ጎሳን መሰረት ያደረገ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በፍጥነት በመግባት ኅብረተሰቡን እያረጋጋሁ ነው አለ

መከላከያ ሰራዊት ጎሳን መሰረት ያደረገ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በፍጥነት በመግባት ኅብረተሰቡን እያረጋጋሁ ነው አለ። መከላከያ ሚኒስቴር ይህንን የተናገረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የሚኒስቴሩን የ6 ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው። የመከላከያ ሚኒስትሯ ኢንጂነር አይሻ መሐመድ እንዳሉት፤ የመከላከያ ሰራዊትን ብቁና ገለልተኛ ለማድረግ ባለፉት 6 ወራት የአሰራርና የአደረጃጀት […]

ሃገር አቀፍ የመጠጥ ውኃ፣ ሳኒቴሽንና ንጽህና አጠባበቅ ተቋማት ቆጠራ እየተካሄደ ነው

ሃገር አቀፍ የመጠጥ ውኃ፣ ሳኒቴሽንና ንጽህና አጠባበቅ ተቋማት ቆጠራ እየተካሄደ ነው ቆጠራው የውሃ ተቋማትን ሁለንተናዊ ይዞታ ለማወቅ የሚያግዝና አገልግሎት የማይሰጡ የውሃ ተቋማትን በፍጥነት በመጠገን ችግሮቻቸውን ለመፍታት የሚያግዝ ነው ተብሏል። የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው ቆጠራው የሚካሄደው ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን በሚቀጥሉት 15 ቀናት ውስጥ ይጠናቀቃል። ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት የተቋማት ቆጠራ የተጀመረው […]

በማዳጋስካር ምርጫ አንድሪ ራጆሊና ድል ቀንቷቸዋል

በማዳጋስካር ምርጫ አንድሪ ራጆሊና ድል ቀንቷቸዋል አሸናፊና ተሸናፊዎቹ ፕሬዝዳንቶች እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2009 በሚገባ ይተዋወቃሉ፡፡ የአሁኑን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማሸነፍ ያቃታቸው ማርክ ራቫሎማናና ማዳጋስካርን በፕሬዝዳንትነት ይመሩ በነበረበት ወቅት የአሁኑ ባለድል አንድሪ ራጆሊና ደግሞ የአንታናናሪቮ ከንቲባ ነበሩ፡፡ የኋላ ኋላ ግን ራጆሊና ከመከላከያ ሀይሉ ጋር በማበር ራቫሎማናና ከስልጠን እንዲወርዱ የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል ነው የሚባለው ፡፡ ከዚያም ራጆሊና በፈረንጆቹ […]

ሂትሮው አየርመንገድ በድሮን ምክንያት በረራ አቋርጦ ነበር

ሂትሮው አየርመንገድ በድሮን ምክንያት በረራ አቋርጦ ነበር በምእራብ ለንደን በሚገኘው የሂትሮው አየር መንገድ አቅራቢያ ድሮን በመታየቱ  ለሰዓታት በረራ እንዲቋረጥ እና መንገደኞች ባሉበት እዲቆዩ ተደርጎ ነበር፡፡ የአየር መነገዱ ቃል አቀባይ  ከፖሊስ እና ከደህንነት አካላት ጋር  ሁኔታውን እያጠኑት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው መንገደኞቹ ከደህንነት ጋር በተያያዘ ምክንያት ከበረራቸው እንዲዘገዩ ሲነገራቸው የመደናገጥ ስሜት ተፈጥሮባቸው ነበር ፡፡ በወቅቱ በረራው […]

ሃገር በቀል ዕውቀቶች በምርምር አልፈውና በቴክኖሎጂ ተደግፈው ወደ ህብረተሰቡ ለማውረድ የሚያስችል መመርያ ፀደቀ

ሃገር በቀል እውቀቶች በምርምር አልፈውና በቴክኖሎጂ ተደግፈው ወደ ህብረተሰቡ ለማውረድ የሚያስችል መመርያ ማፅደቁን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር አስታወቀ። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመማር መስተማር ስራዎቻቸው በተጨማሪ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ እና ከዛም አልፎ ሀገሪቱን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ግኝቶችን በምርምር ማምጣት ይጠበቅባቸዋል። በሀገሪቱ የሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርስቲዎችም በተወሰነ ደረጃ ይህን አብይ ጉዳይ ለማሟላት ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ይታወቃል። ይሁን እንጂ አብዛኞቹ ዪኒቨርስቲዎች […]

የአየርላንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዮ ቫራድከር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የአየርላንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዮ ቫራድከር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን ጀመሩ አየርላንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊኦ ቫራድካርን  በኢትዮጵያ የሶስት ቀናት ጉብኝት ለማድረግ  አዲስ አበባ የገቡት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ግብዣ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ማርቆስ ተክሌ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዮ ቫራድከር በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ […]

በሀገሪቱ የተከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ሊሰሩ ይገባል ተባለ

በሀገሪቱ የተከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ሊሰሩ ይገባል ተባለ ይህ የተባለው ፓርቲዎች በሀገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸው ሚና ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ውይይት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በምርጫ ህግና በተፎካካሪ ፓርቲዎች መካከል የሚደረጉ ሂደቶች ፣ ደንብና ስርዓቶች ላይ መክረዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ በመድብለ ፓርቲ ላይ የሚሰራው የኒዘርላንድስ  ተቋም በኒዘርላንድ ፓርቲዎች በፖለቲካ ውስጥ ያላቸውን […]

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በታህሳስ ወር 3 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የሚያወጡ ምርቶችን ማገበያየቱን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በታህሳስ ወር 3 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የሚያወጡ ምርቶችን ማገበያየቱን አስታወቀ። የምርት ገበያ 39 ሺህ 240 ቶን ሰሊጥ፤ 27 ሺህ 773 ቶን ቡና  እና 10 ሺህ 995 ቶን  ነጭ ቦሎቄ ነው ማገበያየቱን የገለጸው፡፡ ሰሊጥ ከግብይት መጠኑ 51 በመቶ በመሸፈን የመጀመሪያው ሲሆን፥ በዋጋ ደረጃ ደግሞ ቡና 40 በመቶ በመያዝ ቀዳሚ መሆኑን ጠቅሷል። ቡና […]

አልበሽር ወታደሮቻቸውን በመልካም ቃላት እያባበሉ ነው

አልበሽር ወታደሮቻቸውን በመልካም ቃላት እያባበሉ ነው የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር  በአትባራ አቅራቢያ በሚገኘው ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ጦር ሰራዊታችን ይህን መንግስት በሀይል ለመጣል ከሚያሴሩት ጋር ባለማበሩ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል፡፡ የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልሽር በ30 ዓመት የስልጣን ዘመናቸው እንደ ዘንድሮው ያለ ተቃውሞ ደርሶባቸው አያውቅም፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው ፕሬዝዳንቱ ከተቃውሞ ሰልፈኞች በኩል […]

የታይዋን እና የቻይና  ፍጥጫ ወደ ጦርነት እንዳያመራ አስግቷል

የታይዋን እና የቻይና  ፍጥጫ ወደ ጦርነት እንዳያመራ አስግቷል የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ዥንፒንግ ሰሞኑን በተደጋጋሚ አንዲት ቻይና በሚለው ፖሊሲያቸው ታይዋንን ከእናት ሀገሯ የሚለያት የለም ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ ታይዋን በየትኛውም ጊዜ ከቻይና ወረራ ይፈፀምብኛል የሚል ስጋት እንዲገባት  በር ከፍቷል ነው ተባለው፡፡ ዋሽንግተን ፖስት እንደዘገበው የሰሞኑ የቻይና አዝማሚያ ያላማራት ታይዋን በአዲሱ ዓመት ለቤጂንግ መልዕክት በሚያስተላልፍ መልኩ […]