loading
የኮፓ ዴል ሬይ የፍፃሜ ጨዋታ ነገ ምሽት ይደረጋል፡፡

117ኛው የስፔን ኮፓ ዴል ሬይ ወይንም የስፔን ንጉስ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በነገው ዕለት ምሽት 4፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል፡፡ ግጥሚያው በባርሴሎና እና ቫሌንሲያ መካከል ሲቪያ ውስጥ በሚገኘው በሪያል ቤትስ ቤኒቶ ቪያማሪን ስታዲየም ይደረጋል፡፡ በአሰልጣኝ ኤርኔስቶ ቫልቬርዴ የሚመራው የካታላኑ ቡድን በግማሽ ፍፃሜው ተቀናቃኙን ሪያል ማድሪድ በደርሶ መልስ 4 ለ 1 ድል በማድረግ ለተከታታይ ስድስተኛ የፍፃሜ ጨዋታ ሲበቃ […]

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ደደቢት ከሊጉ መሰናበቱን ሲያረጋግጥ፤ ጊዮርጊስ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት መርሀግብር ጨዋታዎች፤ በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በአዲስ አበባ እና ክልል ስታዲየሞች ላይ ተካሂደዋል፡፡ ትናንት አዲስ አበባ ላይ የምስራቁን ድሬዳዋ ከነማ ያስተናገደው ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 ለ 0 ድል በማድረግ ወደ ድል ጎዳና መመለስ ችሏል፡፡ ፈረሰኞቹ መረብ ላይ ያሳረፏቸው ሁለት ግቦች በተከላካይ መስመር ተሰላፊው አስቻለው ግርማ የፍፁም ቅጣት ምት ጎሎች ተገኝተዋል፡፡ የመጀመሪያው አጋማሽ […]

ዛማሊክ የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ አሸናፊ ሆነ፡፡

የ2018/19 የቶታል ካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ የመልስ ግጥሚያ ትናንት ምሽት ግብፅ ላይ ተካሂዷል፡፡ የፍፃሜው ጨዋታ ደግሞ ግብፁ ኤል ዛማሊክ እና የሌላኛዋ ሰሜን አፍሪካዊት ሀገር ሞሮኮ ተወካይ ሬነሳንስ ስፖርቲቭ ዴ ቤርካኔ መካከል ዛማሊክ በመለያ ፍፁም ቅጣት ምት 5 ለ 3 በመርታት በታኩ የመጀመሪያውን የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ አሳክቷል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች ባለፈው ሳምንት ሞሮኮ ላይ የመጀመሪያ ግጥሚያቸውን አድርገው፤ […]

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና የእስልምና ኡለማዎች የኢፍጣር የእራት ግብዣ አደረጉ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና የእስልምና ኡለማዎች የኢፍጣር የእራት ግብዣ አደረጉ፡፡