loading
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የደህንነት መኮንኖች ተመረቁ።

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የደህንነት መኮንኖች ተመረቁ በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የክንፈ ብሄራዊ ደህንነት ጥናት ሰልጣኞች የምረቃ ስነስርዓት የተካሄደው  ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በተገኙበት ነው። በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ እንደተናገሩት ተመራቂ የደህንነት መኮንኖች የኢትዮጵያን የደህንነት ዋስትና ለማረጋገጥ መስራት ይጠበቅባቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሕመድ ተመራቂዎቹ ታማኝነታቸው ለህዝብና ለሀገር በመሆኑ ኃላፊነታቸውን በከፍተኛ ሙያዊ ብቃት […]

ሰባት ኪሎ ወርቅና በርካታ ዶላር በኮንትሮባንድ ሊገባ ሲል ተያዘ

ክብደቱ ሰባት ኪሎ ግራም የሚመዝን ወርቅና ከፍተኛ መጠን ያለው የዉጭ ሃገር ገንዘብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ። ይኸው ወርቅና ገንዘብ የተያዘው በቶጎ ዉጫሌ ኬላ ላይ በሚሰሩ የጉምሩክ ሰራተኞች ሲሆን በወንጀሉ የተጠረጠሩ አራት ኮንትሮባንድ ነጋዴዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል። ሚኒስቴሩ የተያዘውን ገንዘብ መጠን  ቆጠራው ካለቀ በኋላ አሳውቃለሁ ብሏል።

ጠቅላይሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በገቢዎች ሚኒስቴር ቅርንጫፍ የድንገቴ ጉብኝት አደረጉ

ጠቅላይሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በገቢዎች ሚኒስቴር ቅርንጫፍ የድንገቴ ጉብኝት አደረጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የድንገቴ ጉብኝታቸውን በመቀጠል በፌዴራል የመካከለኛ ገቢ ግብር ከፋዮች ቢሮ በመጎብኘት ገለጻ ተደርጎላቸዋል። ከቢሮው ሰራተኞች ጋር እንዲሁም ግብር ለመክፈል እየተጠባበቁ ከነበሩ ግብር ከፋዮች ጋር ተገናኝተዋል። ከሳምንት በፊት ከሚኒስትር መስሪያ ቤቶችና ተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር የአፈጻጸም ግምገማዎች በተካሄደበት ወቅት እንደተገለፀው የመንግስት ተቋማትና ሰራተኞች የሚጠበቅባቸውን […]

የምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እያወያየ ነው

የምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እያወያየ ነው ቦርዱ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚኖረውን ግንኙነት እና በተናጠል የሚያደርጓቸውን እንቅስቃሴዎች የሚገዛ የአሰራር ስርአት ቃል ኪዳን እና መርሆችን የያዘ ሰነድ እና አጀንዳ አዘጋጅቶ ነው ፓርቲዎችን እያወያ ያለው፡፡ በሰነዱ ፓርቲዎች ህገ መንግስቱን መሰረት ባደረገ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ፣ ሃይልን መጠቀም የመንግስት ብቻ ስልጣን መሆኑን ፣ የፓርቲ አመራሮች እና  አባላት ወይም ደጋፊዎች በምንም ሁኔታ […]

የግብፅ ፓርላማ የአልሲሲን ስልጣን ለማራዘም ህገ መንግስት ሊያሻሽል ነው፡፡

የግብፅ ፓርላማ የአልሲሲን ስልጣን ለማራዘም ህገ መንግስት ሊያሻሽል ነው፡፡ የግብፅ ሀገ መንግስት የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ከሁለት ተከታታይ ዓመታት በላይ በስልጣን እንዳይቆይ ይደነግጋል፡፡ አሁን ግን የግብፅ ምክር ቤት የፕሬዝዳንቱን ስልጣን ለማራዘም የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ቀርቦለት ከተወያየ በኋላ ከአንድ አምስተኛ በላይ በሆነ ድምፅ አፅድቆተራል፡፡ ሽንዋ እንደዘገበው ይህ አዋጅ በስራ ላይ ከዋለ ፕሬዝዳንት አብደልፈታህ አልሲሲ በፈረንጆቹ 2022 የስልጣን ዘመናቸው […]

ኢትዮጵያ ካለባት 26 ነጥብ 791 ቢሊዮን ዶላር እዳ ውስጥ  በስድስት ወር 9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ካለባት 26 ነጥብ 791 ቢሊዮን ዶላር እዳ ውስጥ  በስድስት ወር 9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር መክፈሏ ተገለጸ የገንዘብ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ከፍተኛ የዕዳ ጫና ካለባቸው የዓለም ሃገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ካለባት አጠቃላይ የውጭ እዳ ውስጥ 9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብሩን የከፈለችው ባለፉት ስድስት ወራት ነው። የሚኒስቴሩን የስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተነገረው በተያዘው […]

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሲጋራ ማጨሻ ስፍራን የሚገድብና አልኮልን በብሮካስት መገናኛ ብዙሃን ማስተዋወቅን የሚከለክል አዋጅ አፀደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሲጋራ ማጨሻ ስፍራን የሚገድብና አልኮልን በብሮካስት መገናኛ ብዙሃን ማስተዋወቅን የሚከለክል አዋጅ አፀደቀ። ምክር ቤቱ አዋጁን ያጸደቀው በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 24ኛ መደበኛ ስብሰባው ነው ። በፀደቀው አዋጅ መሰረት  በመስሪያ ቤቶች፣ በጤና ተቋማት እና የወጣቶች መዝናኛዎች በሚገኙባቸው አከባቢዎች 100 ሜትር ርቀት ውስጥ ሲጋራ ማጨስ ክልክል መሆኑ ተደንግጓል። ከዚህ በተጨማሪም አዋጁ ማንኛውንም የአልኮል […]

የየመን ተዋጊ ሀይሎች አዲስ ውይይት ጀመሩ፡፡

የየመን ተዋጊ ሀይሎች አዲስ ውይይት ጀመሩ፡፡ የየመን መንግስት እና የሁቲ ሚሊሻዎች ተወካዮች በዮርዳኖስ ኦማን ተገናኝተው በእስረኞች  ልውውጥ ዙሪያ መምከር ጀምረዋል፡፡ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው ውይይቱ ከእስር ተለቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው የሚቀላቀሉ እስረኞን ከመለዋወጥ ባሻገር ለቀጣይ ፖለቲካዊ ንግግር ያለው ፋይዳ ትልቅ ነው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ርድጅት የየመን ልዩ ልኡክ ማርቲን ግሪፊትዝ እና የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፕሬዝዳንት […]