loading
በነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ እሳት ተቀሰቀሰ

በነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ እሳት ተቀሰቀሰ። በደቡብ ክልል አርባ ምንጭ ዞን የሚገኘው የነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ ትናንት ማምሻውን መነሻው ያልታወቀ ሰደድ እሳት መቀስቀሱ ታውቋል። ሰደድ እሳቱ በተለይም የእግዜር ድልድይ የሚሰኙትን ሰንሰለታማ ተራሮች እየተዛመተ ነው ተብሏል። በአካባቢው የሚገኙ የዓይን እማኞች እንደተናገሩት  በፓርኩ የተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት በንፋስ ምክንያት በስፋት በመዛመት ላይ ሲሆን ጉዳቱን ለመቀነስ የመከላከያ ሰራዊት አባላት […]

የአዴፓ አዲስ አርማ ይፋ ሆነ

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) አዲሱን አርማውን ትናንት ይፋ አድርጓል ፓርቲው የአርማ ለውጥ ውሳኔውን ያሳለፈው ባለፈው መስከረም ወር ባካሄደው 12ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ እንደነበር ይታወሳል።

አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ታደሰ ካሳ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የ14 ቀን ቀጠሮ ተሰጣቸው

አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ታደሰ ካሳ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የ14 ቀን ቀጠሮ ተሰጣቸው፡፡ ጉዳዩ በአዲስ አበባ እንዲታይና ዋስትና እንዲሰጣቸው ያቀረቡት ጥያቄም ውድቅ ሆኗል፡፡ አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ታደሰ ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ በውጭ ሆነው እንዲከራከሩና ጉዳዩ አዲስ አበባ እንዲታይላቸውም ጠይቀዋል፡፡ […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ   ጠቅላይ ሚኒስትር ሚር ዐቢይ አሕመድ የአውሮፓ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጣሊያን የጀመሩትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ስዊዘርላንድና ቤልጂየምን በማካለል ተጠናቅቋል፡፡ በጉብኝቱም ከተለያዩ አገራት መሪዎችና የቢዝነስ አንቀሳቃሾች ጋር በመምከር የሁትዮሽ ግንኙነትን ከማጠናከር ባለፈ ኢትዮጵያን በኢንቨስትመንትና ማገዝ የሚያስችሉ ስምምነቶች ተፈርመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአውሮፓ ህብረት […]

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስትና ኦነግ ተኩስ ለማቆም ተስማሙ። የኦነግ ሠራዊት ትጥቅ ፈትቶ ወደ ካምፕ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስትና ኦነግ ተኩስ ለማቆም ተስማሙ። የኦነግ ሠራዊት ትጥቅ ፈትቶ ወደ ካምፕ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል። ሁለቱም አካላት ስምምነቱን የፈጸሙት አምቦ ላይ በተካሄደው የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና የኦነግና የእርቀ ሠላም ጉባዔ ላይ ነው። በስምምነቱ የኦነግ ሠራዊት በ20 ቀናት ውስጥ ትጥቅ ፈትቶ ወደ ካምፕ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል። በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል እርቅ ለማውረድ በአዲስ አበባ በተካሄደው ጉባኤ […]

የሀገር ሽማግሌዎቹ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት ተስማሙ

የሀገር ሽማግሌዎቹ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት ተስማሙ። ሰሞኑን በአፋርና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት ለመፍታት የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች መስማማታቸው ተገለጸ። በቅርቡ በሁለቱ ክልሎች የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣  የሰላም ሚኒስቴር ዴኤታና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በውይይቱም የተፈጠረውን ግጭት  ለመፍታት የሁለቱ ክልሎች የሃይማኖት መሪዎችና […]

በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ አምባሳደሮች በሃገሪቱ የሚካሄደውን የለውጥ ሂደት እንደሚደግፉ አስታወቁ

በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ አምባሳደሮች በሃገሪቱ የሚካሄደውን የለውጥ ሂደት አእንደሚደግፉ አስታወቁ።   በኢትዮጵያ የተጀመረውን የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ለውጥ እንደሚደግፉ በአገሪቱ አዲስ የተሾሙ የስምንት አገራት አምባሳደሮች  ገለፁ። አምባሳደሮቹ ይህንን የተናገሩት በብሄራዊ ቤተ መንግስት  ቀርበው ለፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት ነው። አዲስ ተሿሚዎቹ  የካናዳ፣የቱርክ፣ የሴራሊዮን፣ የኢኳቶሪያል ጊኒ፣ የስሎቫኪያ ሪፐብሊክ፣ የሰርቢያ እንዲሁም ተቀማጭነታቸው በካይሮ እና ናይሮቢ ያደረጉት […]

በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ ወረቀት አልባ የህክምና ና የጤና መረጃ ሥርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው ተባለ

በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ ወረቀት አልባ የህክምና ና የጤና መረጃ ሥርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው ተባለ በኢትዮጵያ  በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ ወረቀት አልባ የህክምና ና የጤና መረጃ ሥርዓት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የዲጂታይላይዜሽን የጤና አገልግሎት ሥርዓትን ያስተዋወቀበትን መርሐ ግብር በመቀሌ ከተማ ባካሄደበት ወቅት እንዳስታወቀው ሥርዓቱ በሙከራ ደረጃ በትግራይ፣ በአማራ፣በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች በሚገኙ 1ሺህ60 የጤና ተቋማት ላይ ተጀምሯል፡፡ […]

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ሎጀስቲክስ አገልግሎት ለደንበኞቼ ቀልጣፋ አገልግሎት ተዘጋጅቻለሁ አለ

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ሎጀስቲክስ አገልግሎት ለደንበኞቹ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱን ገለጸ ድርጅቱ 13 ዘመናዊ የኮንቴይነር መጫኛና ማውረጃ ማሽኖችን ለስራ ማዘጋጀቱ ተነግሯል። የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት 95 በመቶው የሀገሪቱ ገቢና ወጪ ንግዶች ይከናወኑበታል፡፡ በሰባት ደረቅ ወደብና ተርሚናሎች ነው እያገለገለ የሚገኘው፡፡ ድርጅቱ በ11 የኢትዮጵያ መርከቦች ከ306 ያላነሱ የተለያዩ ሀገራት ወደቦችን በማዳረስ ዕቃዎችን ያጓጉዛል፡፡ የድርጅቱ የኮርፖሬት […]