loading
ኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በአልጋርቭ ዋንጫ ውድድር ላይ ትዳኛለች ተባለ

ኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በአልጋርቭ ዋንጫ ውድድር ላይ ትዳኛለች ተባለ አትዮጵያዊቷ ዋና ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በ2019ኙ የአልጋርቭ ዋንጫ ካፍን ከሚወክሉ ዳኞች መካከል ተካትታለች ተብሏል፡፡ የአልጋርቭ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 27 እሰከ መጋቢት 06/2019 በፖርቱጋል አስተናጋጅነት በሚካሄደው ውድድር በዋና ዳኝነት ዘጠኝ ዋና ዳኞች ከዘጠኝ የተለያዩ ሀገራት እንዲሁም 18 ረዳት ዳኞች ከአስራ አራት ሀገራት ተመራጭ ሆነዋል፡፡ የዓለም አቀፉ […]

ጣሊያን እና ፈረንሳይ በአፍሪካ ጉዳይ እየተነታረኩ ነው::

ጣሊያን እና ፈረንሳይ በአፍሪካ ጉዳይ እየተነታረኩ ነው:: የቀድሞዎቹ ጥብቅ ወዳጆች ፈረንሳይ እና ጣሊያን በመካከላቸው ያለው ግንኙነት ነፋስ ገብቶበታል የሚለው ወሬ በስፋት እየተሰማ ነው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው ይህ ነገር የተፈጠረው ባለፈው ዓመት በጣሊያን አዲስ የጥምር መንግስት ከተመሰረተ ጀምሮ ነው፡፡ ፈረንሳይ በአፍሪካ የምታራምደውን ፖሊሲ የአንድ ወገን ተጠቃሚነትን አጉልቶ የሚያሳይ ነው ስትል ጣሊያን ትከሳለች፡፡ የኢማኑኤል ማክሮን አስተዳደር በሊቢያ ሰላም […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በዳቮስ ኢኮኖሚክ ጉባኤ ላይ ንግግር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በዳቮስ ኢኮኖሚክ ጉባኤ ላይ ንግግር አደረጉ በንግግራቸው በኢትዮጵያ ስለተጀመሩት ለውጦች ዳሰሳ አድርገዋል በአለም ኢኮኖሚ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ጠቅለዓይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መደመር ያለፈ ፀጋችንን እንደገና የመፈተሸና ወደ ብልጽግና የመመለስ መርኅ ነው ብለዋል። ዴሞክራሲ፣ ምጣኔ ሀብታዊ ማሻሻያና ቀጠናዊ ውሕደት የለውጥ ምሕዋራችን የቆመባቸው ዓምዶች ሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሕገ-መንግሥታዊ ቃል-ኪዳንን […]

ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አመት የአለም የኢኮኖሚ ጉባኤን እንድታስተናግድ ስምምነት ላይ ተደረሰ

ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አመት የአለም የኢኮኖሚ ጉባኤን እንድታስተናግድ ስምምነት ላይ ተደረሰ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአለም የኢኮኖሚ ጉባኤ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ክላውስ ሻዋብ ጋር በተወያዩበት ወቅት ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ 2020 የአለም የኢኮኖሚ ጉባኤን እንድታስተናግድ ተስማምተዋል። እንደጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት መግለጫ ጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ አህመድ እና ፕሮፌሰር ሻውብ ቁልፍ የሆኑ ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን ለመፍታት በንግድ፣ በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ […]

ሶስተኛው የኢጋድ እና የአውሮፓ ህብረት የሚኒስትሮች የጋራ ስብሰባ ተካሄደ

ሶስተኛው የኢጋድ እና የአውሮፓ ህብረት የሚኒስትሮች የጋራ ስብሰባ ተካሄደ ሶስተኛው የኢጋድ እና የአውሮፓ ህብረት የሚኒስትሮች የጋራ ስብሰባ በትናንተናው በቤልጂየም ብራሰልስ ተካሂዷል። ሁለቱ ወገኖች በጋራና በትብብር በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ለቀጠናው ያለውን አዎንታዊ ጠቀሜታ፣ የሶማሊያ እንዲሁም የደቡብ ሱዳን የሰላም ሂደት ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ ውይይት አድርገዋል። በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ውህደት […]

የአቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ጉዳይ በክልሉ ፍርድ ቤት እንደሚታይ ተገለፀ

የአቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ጉዳይ በክልሉ ፍርድ ቤት እንደሚታይ ተገለፀ፡፡ በጥረት ኮርፖሬት ላይ ከደረሰ የሀብት ብክነት ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ ጉዳይ በክልል ፍርድ ቤት እንደሚታይ የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን ገለፀ። የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዝግአለ ገበየሁ  ሁለቱ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር […]

የመንግስት ንግድ ቤት ተከራዮች የቤቶች ኮርፖሬሽን የወሰነውን የዋጋ ጭማሪ  በድጋሚ እንዲያጤንላቸው መንግስትን ጠየቁ

የመንግስት ንግድ ቤት ተከራዮች የቤቶች ኮርፖሬሽን የወሰነውን የዋጋ ጭማሪ  በድጋሚ እንዲያጤንላቸው መንግስትን ጠየቁ፡፡ ነጋዴዎቹ ይህን የጠየቁት ዛሬ በግሎባል ሆቴል አዳራሽ ባደረጉት የጋራ ውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡ በውይይታቸውም ለቤት ኪራይ የተወሰነው ውሳኔ በበቂ ጥናት ላይ ያልተመሰረተ እና በቂ ባለሙያዎችን ያሳተፈ አይደለም ብለዋል፡፡ አቋማችን ጭማሪው አይደረግ የሚል ሳይሆን ተመጣጣኝ ጭማሪ ይደረግ የሚል ነው ብለዋል፡፡ ውሳኔው ነጋዴዎቹ ከቤታቸው […]