loading
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበርሚንግሃም ዳይመንድ ሊግ በነገው ዕለት ከሰአት በኋላ በተለያዩ ሩጫዎች ይካፈላሉ፡፡

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበርሚንግሃም ዳይመንድ ሊግ በነገው ዕለት ከሰአት በኋላ በተለያዩ ሩጫዎች ይካፈላሉ፡፡ በሴቶች 1500 ሜ በ10:22 ሰዓት፤ አክሱማይት እምባዬ ጉዳፍ ፀጋዬ አልማዝ ሳሙኤል በወንዶች 3000 ሜ መሰናክል በ10:33 ሰዓት፤ ጫላ ባዮ በሴቶች 3000 ሜ. በ10:49 ሰዓት፤ እጅጋየሁ ታዬ

ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ፡፡

ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ፡፡ ኢቢሲ እንደዘገበዉ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ በነዳጅ ቦቴ ሲዘዋወር የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡ በዚህም 1051 ሽጉጦች፣ መጠናቸው ያልታወቁ ጥይቶች እና ወደ ውጪ ሊወጣ የነበር መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ ቁጥጥር ስር መዋሉን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡

ሳልቫ ኪር ኤርትራን ሊጎበኙ ነው፡፡

ሳልቫ ኪር ኤርትራን ሊጎበኙ ነው፡፡ የኤርትራ ፕሬስ እንደዘገበው የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር አስመራን የመጎብኘት እቅድ ይዘዋል፡፡ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት ደቡብ ሱዳን ራሷን ችላ ሀገር መሆኗን በይፋ ስታውጅ ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጁባ በተገኙበት ወቅት ነበር፡፡

ለአዲስ ዓመት ከውጪ ሀገር ለሚመጡ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች 25 በመቶ የጤና አገልግሎት ቅናሽ ይደረግላቸዋል ተባለ፡፡

ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሰው መግለጫ ከ ነሃሴ 14 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የሚመጡ ኢትዮጲያዉያን ዲያስፖራዎች የአገልግሎት ቅናሹ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡ በጤና ጥበቃ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ተገኔ ረጋሳ በፌደራል እንዲሁም በክልል የጤናውን ዘርፍ በተመለከተ ለሚመጡት ዲያስፖራዎች መረጃ እንዲሰጥ የተዋቀረ የድንገተኛ አስተባባሪ ቡድን መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች ወደ ሃገር ቤት ሲመጡ ከሚያገኙት የጤና አገልግሎት ባሻገር […]

የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ኮፊ አናን በ80 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ።

የኖቤል ተሸላሚ የነበሩት አናን እአአ በ1938 በጎልድ ኮስት ጋና ነበር የተወለዱት። ኮፊ አታ አናን ሙሉ ስማቸው ሲሆን አካን በሚባል ቋንቋ የመጀመሪያ ስማቸው ‘‘በዕለተ አርብ የተወለደ’’ ማለት ሲሆን አታ ማለት ደግሞ ‘‘መንትያ’’ ማለት ነው። በጋና እና አሜሪካ ትምህርታቸውን ከተከታተሉ ሲሆን የመጀመሪያ ስራቸውን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በመጀመር ለአርባ ዓመታት አገልግለዋል። የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ለመሆንም በቅተዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የመንጋ ፍትህ እና አላስፈላጊ ሁከት ተቀባይነት የሌለው እና የህግ የበላይነትን አደጋ ውስጥ የሚጥል መሆኑን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በ11ኛው እነ 12ኛው ዙር የሰለጠኑ የመከላከያ መኮንኖችን ባስመረቁበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ድርጊቱ የህግ የበላይነትን የሚነድ በመሆኑ በአስቸካይ ሊቆም እንደሚገባው ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በተለይም ወጣቱ የተሳሳተ መረጃን መሰረት በማድረግ ለህግ ቅድሚያ ሳይሰጥ የሚፈጽማቸው ድርጊቶች እየተገነባች ያለችን ሃገር ከማፍረስ ውጭ ዋጋ እንደሌለውም ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ የህግ የበላይነት ለአንድ […]

ከሁለት ሳምንት በፊት ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ፍቃድ ውጭ ገብተዋል የተባሉ አርባ አምስት የፌደራል ፖሊስ ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል አባላት ከመቀሌ እንዲመለሱ ተደርገዋል

አባላቱ በአሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የመጡበት አላማም እስኪታወቅ ድረስ እንቅስቃሴያቸው ተገድቦ በፌደራል ካምፕ ውስጥ እንዲቆዩ ተደርጎ ነበር። የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳኢ ኃለፎም ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ የፀጥታ ችግር ባለመኖሩ የፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል አስፈላጊ አለመሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጨምረውም ክልሉ ድጋፍ የሚጠይቀው ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ ነገር ሲያጋጥም ወይም […]

ከስድስት ወራት በኋላ የሁሉም የስኳር ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡

ዶክተር አብይ ይህንን ያሉት በባህርዳር ከተማ ከብአዴን አመራሮች ጋር ባደረጉት ምክክር ላይ ነው፡፡ ባለፉት 9 ወራት የተሻለ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ኢኮኖሚያዊ ለውጦችን ለማምጣት ውጤታማ ተግባራት ተከናዉነዋል ብለዋል፡፡ በሀገሪቱ የተሻለ መግባባት ለመፍጠርም ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ጋር የነበረውን ግንኙነት የማስተካከልና በሀይማኖቶች ውስጥ የነበረውን መከፋፈል የማጥፋት ስኬታማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ በኢኮኖሚ ረገድም የውጭ ምንዛሬ በቤታቸው ያከማቹ ዜጐች ወደ ባንክ […]

ባለፉት 24 ዓመታት በኢትዮጵያ በትምህርትና ስልጠና ሥርዓት በታዩ ችግሮች ዙርያ ዛሬ ውይይት ይደረጋል

የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ ከዛሬ ጀምሮ የሚደረገው የውይይት መድረክ ዋነኛ ዓላማ ለፍኖተ-ካርታው ዝግጅት እንዲረዳ በተዘጋጀው የመጀመሪያ ደረጃ ረቂቅ ጥናት ዙሪያ ውይይት በማድረግ ለፍኖተ-ካርታው ዝግጅት የሚረዳ ተጨማሪ ግብዓት ለማሰባሰብ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ የማሻሻያ ሀሳቦች ዙሪያ በሚደረገው ውይይት በተሳታፊዎች የሚቀርቡ ተጨማሪ የማሻሻያ ሀሳቦች በቂ ውይይት ከተደረገባቸውና መግባባት ከተደረሰባቸው በኋላ ለ15 ዓመታት […]