loading
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ በከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ሙስና ወንጀል በተጠረጠሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜን ፈቀደ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ በከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ሙስና ወንጀል በተጠረጠሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜን ፈቀደ

በካራባዎ ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ቼልሲ ከ ቶተንሃም ይፋለማሉ

አርትስ ስፖርት 11/04/2011 በካራባዎ ዋንጫ ትናንት ምሽት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተካሂደዋል፤ በሰሜን ለንደን ደርቢ አርሰናል በፍላይ ኢምሬትስ ከቶተንሃምተጫውተው እንግዳው ክለብ በሰን ሁንግ ሚን እና ደሊ አሊ ጎሎች 2 ለ 0 በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቅሏል፡፡ በስታንፎርድ ብሪጅ ቼልሲ ከ በርንማውዝ ተጫውተው፤ ሰማያዊዎቹ በኢዲን ሃዛርድ ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜውተዋህዷል፡፡ ማክሰኞ ምሽት ማንችስተር ሲቲና ቡርቶን አልቢዮን ተጋጣሚዮቻቸውን በመርታት ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፈዋል፡፡ በግማሽ ፍፃሜ የዕጣ ድልድል ቶተንሃም ከ ቼልሲ በለንደን ደርቢ ሲገኛኑ፤ ማንችስተር ሲቲ ከ ቡርቶን አልቢዮን ይጫወታሉ፡፡ ዙሩ የደርሶ መልስ ግጥሚያ የሚኖረው ሲሆን የመጀመሪያ ጨዋታዎች ጥር 8 እና የመልስ ፍልሚያዎች ጥር 22/2019 ይደረጋሉ፤ ማንችስተርሲቲ እና ቶተንሃም በሜዳቸው የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡