loading
ኤርትራ የነፃነት ትግል የጀመረችበትን 57ኛ ዓመት በዓልን ነገ ታከብራለች፡፡

አርትስ 25/12/2010 የዘንድሮው በዓል አገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር የሰላምና የወዳጅነት ስምምነት ካደረገች በኋላ የሚከበር በመሆኑ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው እንደሆነ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ገልጸዋል ሲል ኢ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡

በደቡብ አፍሪካ ስዌቶ ግዛት የአንድ ኢትዮጵያዊ ህይወት አለፈ

አርትስ 25/12/2010 በደቡብ አፍሪካ ስዌቶ ግዛት ውስጥ የሌላ አገር ዜጎች ላይ እየተፈጸመ ካለው ጥቃት ኢትዮጰያውያን ራሳቸውን እንዲጠብቁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ ፡፡ በእስከአሁኑ ጥቃት አንድ ኢትዮጵያዊ ህይወቱ ሲያልፍ አንድ ሌላ ኢትዮጵያዊ ደግሞ ጉዳት ደርሶበት ሃኪም ቤት እያገገመ ይገኛል ብሏል የውጭ ጉዳይ ፅ/ቤት ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ፡፡ ደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የኢፌዲሪ ኤምባሲ ከአገሪቱ መንግስት ጋር […]

አርቲስት ታማኝ በየነ አዲስ አበባ ገብቷል።

ጎንደር የተወለደው ታማኝ ከ22 ዓመታት የውጭ ሀገር ቆይታ በኋላ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ አቀባበል ተደርጎለታል። አርቲስቱ ወደ ብሄራዊ ቤተ መንግስት ያሄዳል፡፡በቤተ-መንግስት ከሀገሪቱ መሪዎች ጋር ይገናኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በብሄራዊ ትያትርም ቆይታ ያደርጋል፡፡ ነገ ደግሞ በሚሊንየም አዳራሽ አድናቂዎቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት የእንኳን ደህና መጣህ ልዩ ዝግጅት ይኖራል ፡፡ አቀባበሉ በባህርዳርም ይቀጥላል።