loading
የኢትዮጲያ ሙስሊሞች አንድነት እና ሰላም ላይ ያተኮረ የኢለሞች አንድነት እና ትብብር ጉባኤ ተካሄደ።

የአንድነት ጉባኤው የተካሄደው በኢትዮጲያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ አዘጋጅነት ነው፡ሀጂ ዑመር ሰኢድ የኮሚቴው ምክትል ፀሃፊ እንደገለፁት የጉባኤው አብይ አላማ የሀገራችን ሙስሊሞችን አስተባብሮ አንድነቱን ጠብቆ የሚመራ በይዘትም በአደረጃጀትም ጠንካራ እና ሁሉን አቀፍ መሪ ድርጅት የሚቋቋምበት ህግ እና አደረጃጀት የሚያመላክት ምክረ ሀሳብ ማቅረብ እንዲሁም ወደአንድነት መምጣት ነው ብለዋል፡፡ የአንድነት እና ትብብር ኮሚቴው ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዩስን መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ ጎበኙዋቸው፡፡

በጉብኝቱ ላይ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ተገኝተዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩም እንዳሉት አቡነ መርቆርዮስን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በመሆን በመጎብኘታቸው ከፍ ያለ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ወቅት ከአቡነ መርቆርዮስ ጋር ስለይቅርባይነትና ስለፍቅር ተወያይተዋል፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጠቅላይ ሚኒስተሩ አቡነ መርቆርዮስን መኖሪያ ቤታቸው ድረስ ተገኝተው በመጎብኘታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ባለፉት 26 ዓመታት […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 5 የአፍሪካ አየር መንገዶችን በሽርክና ሊያስተዳድር ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንደተናገሩት የጊኒ አየርመንገድን በ49 በመቶ፣የዛምቢያ አየር መንገድን በ45 በመቶ፣ እንደ አዉሮፓዉያን አቆጣጠር በጥቅምት የሚጀምረዉን የቻድ አየር መንገድን በ49 በመቶ ድርሻ በሽርክና ሊያስተዳድር ነዉ፡፡ የዛምቢያና የኢኳቶሪያል ጊኒ አየር መንገዶችን ደግሞ የአስተዳደራዊ ስራዉን እንዲሰራ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት ተቀብሎ በሽርክና ለማስተዳደር መስማማቱን ነዉ አቶ ተወልደ የገለጹት፡፡

ዛሬ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክያትን በጀዋር መሃመድ የሚመራዉ ቡድን የኦሮሚያ የሚያደርገውን ጉብኝቱን ለጊዜው ማቆሙን ኦ ኤም ኤን ዘገበ።

በዛሬዉ ዕለት በሻሸመኔ ከተማ በተፈጠረ መገፋፋትና መረጋገጥ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርከት ያሉ ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን አቶ አዲሱ አረጋ የኦህዴድ የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አስታውቀዋል። አደጋው የደረሰው የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ዳይሬክተር አቶ ጃዋር መሃመድ እና ሌሎች የቡድኑ አባላት አቀባበል ለማድረግ በከተማዋ በተዘጋጀ ስነ ስርዓት ላይ ነዉ። በአደጋውም እስካሁን የ3 ሰዎች ህይወት […]

አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢሶህዴፓ/ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ።

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢሶዴፓ/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባለፉት ሶስት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጥልቅ ግምገማ ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው አቶ አህመድ ሽዴ ሊቀ መንበር አድርጎ የመረጠው። የኢሶዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ አህመድ ሽዴን በሙሉ ድምጽ በሊቀ መንበርነት መምረጡም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢሶዴፓ/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባለፉት ሶስት ቀናት ስብሰባው በክልሉ ተፈጥሮ በነበሩው ሁኔታ […]

የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ልኡክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል።

በግንባሩ ቃል አቀባይ አቶ አዳኒ አብዱልቃድር ሄርሞጌ የተመራው እና 3 አባላትን ያለው ልኡኩ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ አቀባበል አድርገዋል። ወደ ሀገር የገባውን ልኡክ የመሩት አቶ አዳኒ አብዱልቃድር ሄርሞጌ፥ ግንባሩ ወደ ሀገር ቤት ለመግባት የወሰነው የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ […]

የህወሀት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን መቐለ በተካሄደው ሰልፍ ባስተላለፉት መልእክት “ያለን አማራጭ ተከባብሮ መኖር አልያም መበታተን” ማለታቸው ትግራይን ለመገንጠል ከሚል የመነጨ ሳይሆን የሀገሪቱ የፌደራል ስርአት እኩልነትን መሰረት ያደረገ መሆኑ ለመጠቆም የተነገረ ነዉ አሉ።

ህወሀት በዚህ ወር 13ኛ ድርጅታዊ ታሪካዊ የለውጥ ጉባኤ ያካሄዳል ተብሏል፡፡ ሊቀመንበሩ በጉባኤው እስካሁን የተደረጉት የለውጥ እንቅስቃሴዎች ወደተግባር ሊለውጥ የሚችል ብቁ አዲስ ትውልድ ወደ አመራርነት ይመጣል ብለዋል። ህወሓት ህገመንግስትን መሰረት አድርጎ ለሚደረግ የለውጥ ጉዞ ደጋፊ እንጂ እንቅፋት እንደማይሆን ዶክተሩ ተናግረዋል። በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ የሰጡት ሊቀመንበሩ ባለፉት አመታት በሀገሪቱ ከተመዘገቡ የልማት ስኬቶች በተጨማሪ በርካታ ጉድለቶች […]

መኢአድ አንቀጽ 39 እንዲሰረዝ ጠየቀ::

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አገር ለማፍረስ የተቀመጠ ነው ያለውን የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 39 እንዲሰረዝ ጥያቄ አቀረበ፡፡ ፓርቲውን ይህን ጥያቄ በይፋ ያቀረበው ሐሙስ ነሐሴ 3 ቀን 2010 ዓ.ም. ‹‹አገር ለማፍረስ የተቀመጠው አንቀጽ 39 የወለደው ችግር የበርካታ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ ይገኛል፤›› በማለት፣ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ […]

የኢንጂነር ስመኘው ቤተሰቦች የምርመራው ውጤት በምንፈልገው ፍጥነት እየሄደ አይደለም አሉ፡፡

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ላይ መኪናቸው ውስጥ ባልታወቀ ምክንያት ህይወታቸው አልፎ ከተገኘ ሁለት ሳምንታት አለፉ። ቢቢሲ እንደዘገበዉ የኢንጂነር ስመኘው ባለቤት የወ/ሮ ዕሙን ጌታሁን ታናሽ ወንድም የሆነው አካሉ ጌታሁን ”ሃዘናችን እጅግ ከባድ ቢሆንም እየበረታን ነው። ከቀብሩ ጀምሮ መንግሥት እየደገፈን ነው። ምንም ያወጣነው ወጪ የለም” ብሏል። አካሉ ጨምሮም […]

ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳን ጨምሮ 11 የፖሊስ አመራሮች በዋስ ቢለቀቁ እንደማይቃወም አቃቤ ህግ አስታወቀ

ሰኔ 16ቱ የመስቀል አደባባይ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የአመራርነት ክፍተት አሳይተዋል ተብለው ምርምራ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ በዋስ ቢለቀቁ አቃቤ ህግ እንደማይቃወም ገለጸ፡፡ አቃቤ ህግ ምክትል ኮሚሽነሩን ጨምሮ ሌሎች 11 የፖሊስ አመራሮችም በዋስ ቢለቀቁ እንደማይቃወም አስታውቋል፡፡ የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎትም በጉዳዩ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ቀጠሮ መስጠቱ ተገልጿል፡፡ […]