loading
ሱዳንና ኢትዮጵያ የድንበር ቁጥጥርን ለማስወገድ ተስማሙ::

ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር የምታደርገውን ቁጥጥር ለማቆም ቁርጠኛ መሆንዋን አስታውቃለች፡፡ ሱዳን ከውሳኔ ላይ የደረሰችው የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሀፊዝ አብዱል ራህማን ከኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር በካርቱም በገቡት ስምምነት መሰረት ነው፡፡ የሀገራቱን ግንኙነት እንደሚያጠናክር የተነገረለት ስምምቱ እውን የሚሆነውም በሁለቱ ሀገራት የጋራ የቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት እንደሆነ ተነግሯል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካቢኔ ሹም ሽር ሊያካሄድ ነው ተባለ፡፡

ሪፖርተር እንደዘገበዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የካቢኔ አባላት ሹም ሽር ሊያካሂዱመሆኑ እና ከመጠን በላይ በመስፋታቸው ምክንያት ለአሠራር አላመቹም የተባሉ መሥሪያ ቤቶች እንደሚታጠፉ ተነገሯል፡፡ ከፌዴራል መንግሥትና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ አመራሮች፣ እስከ ቀጣዩ ምርጫ ድረስ የካቢኔ አባል ሆነው የሚሠሩ ተሿሚዎች እየመለመሉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተፈጸመውን ድርጊት አወገዘች።

ቤተክርስትያንዋ ሰባት አብያተ ክርስትያናት ሙሉ በሙሉ ተቃጥለው የካህናት ህይዎት ማለፉንም ተናግራለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያሪክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በሶማሌ ክልል በተፈጸመው ድርጊት ሳቢያ የሰው ህይዎት በመጥፋቱ ማዘናቸዉን ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈም የሰላማዊ ሰዎች ህይዎት ማለፉንና በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው፥ በሁኔታው የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል። አሁን ላይ አብረው በኖሩ ወንድማማች ህዝቦች […]

ኡሁሩ ኬንያታ ደቡብ ሱዳኖችን አድንቀዋል፡፡

የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ሀይሎች መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ይበል የሚያሰኝ ሲሉ አሞካሽተውታል፡፡ በደቡብ ሱዳን የሚገኙ ሁሉም የፖለቲካ ሀይሎች ከጦርነት ይልቅ ሰላምን እንደ አማራጭ መውሰዳቸው ብልህነት ነው ያሉት ኬንያታ ሀገራቸው ይሄን የተቀደሰ ሀሳብ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗንም አረጋግጠዋል፡፡ ሱዳን ካርቱም ላይ የተደረገው ስምምነት የፕሬዝዳንት ሳልቫኪር የቀድሞው ምክትላቸውና የአሁኑ ተቀናነቃኛቸው ዶክተር ሪክ ማቻር ወደ […]

በድሬዳዋ ከተማ ከትናንት ጠዋት ጀምሮ በተከሰተው ግጭት የአሥር ሰዎች ህይወት ማለፉን፣ የአካል ጉዳት መድረሱን እና ንብረት መውደሙን ፖሊስስ ገለፀ፡፡

ግጭቱ በተከሰተበት ቀበሌ 09 እና አካባቢው በአሁኑ ሰዓት የተረጋጋ ሁኔታ መኖሩን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ለአርትስ ቲቪ አስታውቋል፡፡ የሰዎች ህይወት ያለፈው ከእሳት ቃጠሎ ጋር በተገናኘ እንደሆነ የገለፀው ፖሊስ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር እያዋልኩ ነው ብሏል፡፡ የሰላም ተምሳሌቷ ድሬ ወደቀድሞ ሰላሟ እንድትመለስ ወጣቶችና የአገር ሽማግሌዎች አሁንም እየሰሩ እንደሆነ የገለፁልን ዋና ሳጅን ባንታለም ግርማ […]

ሳውዲ አረቢያ ካናዳን ጣልቃ ገብነትሽን አቁሚ ብላታለች፡፡

ሪያድ የካናዳን አምሳደር ከሀገሯ እንዲወጡ ትዕዛዝ አስተላልፋለች፤ የንግድ ግንኙነቷንም አቋርጣች፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው የሀገሪቱ መንግስት በሳውዲ የካናዳን አምባሳደር ለማባረር ውሳኔ ላይ የደረሰው ሉዓላዊነቴን የሚጋፋ ጣልቃ ገብነት ተፈጸሞብኛል በሚል ምክንያት ነው፡፡ ካናዳ ሳውዲ አረቢያ ያሰረቻቻውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንድትፈታ ያቀረበችው ጥያቄ ነው በሁለቱ ሀገሮች መካካል የተፈጠረውን አለመግባባት ያመጣው ተብሏል፡፡ የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መስሪያ ቤት በሰጠው […]

የሶማሌ ክልል አዲሱ ፕሬዚዳንት አህመድ አብዲ መሀመድ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሀመድ ኦማር ስልጣን እንዳስረከቡና ሽግግሩም በሰላም እንደተጠናቀቀ ለቢቢሲ ሶማልኛ ተናግረዋል።

የክልሉ አዲሱ ፕሬዚዳንት እንደተናገሩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ስልጣን ለመልቀቅ በመጠየቃቸው የስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አዲሱን የክልሉ ፕሬዚዳንት እንደመረጠም ገልፀዋል። ሰሞኑን ከብዙ ሰዎች ሞት፣ አብያተ ክርስትያናት መቃጠልና ንብረት መውደም ጋር ተያይዞም በክልሉ የመከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን በክልሉ ከነበረው አለመረጋጋትና ተቃውሞዎች ጋር ተያይዞም በማዕከላዊ መንግሥት ግፊት ምክንያት አብዲ ኢሌ ከስልጣን እንደወረዱ ብዙዎች አስተያታቸውን ቢሰጡም አዲሱ ፕሬዚዳንት ሲንከባለል […]

የዚምባብዌ መንግስት የተቋዋሚ አባላትን ፍርድ ቤት አቆመ፡፡

ተቃዋሚዎቹ የተከሰሱት በዚምባቡዌ በተካሄደዉ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ኤመርሰን ምናንጋግዋ ማሸነፋቸዉን ተከትሎ በሀገሪቱ በተቀሰቀሰዉ አመጽ እጃችሁ አለበት ተብለዉ ነዉ ፡፡ የኬንያዉ ዴይሊ ኔሽን እንደዘገበዉ 27 የተቃዋሚ ፓርቲ አበላት ላይ የዚምባብዌ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል፡፡ ከተከሳሾቹ መካከል ዘጠኙ ሴቶች ናቸዉ ፡፡ ፕሬዝደንቱ በአንድ በኩል የሙቭመንት ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ ፓርቲን ለአመጹ መነሻ ነዉ በማለት ሲከሱ በሌላ በኩል በግርግሩ ሳቢያ […]

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን በሶማሌ ክልል በጅግጅጋ በተከሰተዉ ግጭት በደረሰዉ የሰዉ ህይወት መጥፋትና ንብረት መዉደም ማዘንዋን ገለጸች፡፡

ቤተክርስትያንዋ ሀዘንዋን የገለጸችዉ ዛሬ የተጀመረዉን የፍልሰታን ጾም አስመልክቶ ለአርትስ ቲቪ በላከችዉ መግለጫ ነዉ፡፡ በመግለጫዉ የካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀጳጳስ ካርዲናል ብርሃነየሱስ እንዳስታወቁት የፍልሰታ ጾም የተጀመረዉ ቤተክርስትያናችን 19ነኛዉን የአመሰያን ጉባኤ በስኬት ባስተናገደች ማግስት በመሆኑ ተደስተናል ብለዋል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ አካባቢዎች በተከሰተዉ ግጭት ምክንያት የሰዉ ህይወት በማለፉ ሀዘን ተሰምቶናል፡፡ቤተክርስትያንዋም ለሰላም ትጸልያለች ብለዋል፡፡ ካርዲናሉ በመግለጫቸዉ በአሁኑ ወቅት ምእመናንም በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉና […]