loading
ፖሊስ በኔታናያሁ ላይ ምርመራውን ቀጥሏል፡፡

ፖሊስ በኔታናያሁ ላይ ምርመራውን ቀጥሏል፡፡
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤናሚን ኔታንያሁ በሙስና ከተጠረጠሩባቸው ወንጀሎች በአንዱ ዛሬ ፖሊስ ለጥያቄ ጠርቷቸው ነበር፡፡
ሮይተርስ እንደዘገበው የእስራኤል ፖሊስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ምርመራ የሚያደርገው ከሀገሪቱ የቴሌኮም ኩባንያ ጋር የልተገባ ግንኙነት ነበራቸው በሚል ነው፡፡
ፖሊስ እንደሚለው ኔታናያሁ ለቴሌኮም ኩባንያው የሚጠቅሙ አሰራሮች እንዲተገበሩ ትእዛዝ በመስጠት በምላሹ በዌብሳይቱ ስለሳቸውና ስለ ባለቤታቸው መልካምነት ሰፊ ሽፋን እንዲሰጥ ተስማምተዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *