loading
ያለ ህጋዊ ሰነድ ወደ ውጪ ሊወጣ የነበረ የባህር ዛፍ አጠና በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

ያለ ህጋዊ ሰነድ ወደ ውጪ ሊወጣ የነበረ የባህር ዛፍ አጠና በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
ምንም ህጋዊ ሰነድ ሳይኖረው እና ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና መያዙን የጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት አስታውቋል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃው አቶ ተስፋዬ አረጋዊ በተባለ አሽከርካሪ አማካኝነት በሰሌዳ ቁጥር 79780/00054 በሆነ ተሳቢ መኪና ተጭኖ ሊወጣ ሲል ቶጎጫሌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጉምሩክ ባለሙያዎችና በመከላከያ ሰራዊት አባላት የጋራ ጥረት ሊያዝ ችሏል፡፡
በተያያዘም በቀን 20/05/11 ከምሽቱ 3፡30 ላይ አቶ ሙሴ ዘካሪያ የተባለ ተጠርጣሪ 2 ግራም የሚሆን ሜርኩሪ መሰል ማዕድን በሶማሌ ክልል አድርጎ ወደ ሶማሌ ላንድ ሊያስወጣ ሲል በቁጥጥር ስር ማዋሉን የጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት አስታውቋል፡፡

ምንጭ፤-ገቢዎች ሚኒስቴር

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *