loading
የፈረንሳይ መንግስት በነዳጅ ላይ ሊጥል ያሰበውን ታሪፍ ለጊዜው አዘግይቶታል

የፈረንሳይ መንግስት በነዳጅ ላይ ሊጥል ያሰበውን ታሪፍ ለጊዜው አዘግይቶታል

አርትስ 25/03/2011

 ፓሪስ ቢጫ ሰደርያ በለበሱ የተቃውሞ ሰልፈኞች መጨናነቅ ከጀመረች ሁለት ሳምንታትን አስቆጥራለች፡፡

ምክንያታቸው ደግሞ የፈረንሳይ መንግስት በነዳጅ ምርቶች ላይ ቀረጥ ሊጥል ነው የሚል ዜና መሰማቱ  ነው፡፡

ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው ሰልፈኞቹ በየጎዳናው ያገኙትን ቁሳቁስ ሁሉ ሲያቃጥሉ እና ከፖሊስ ጋር ግጭት ውስጥ ሲገቡ ተስተውለዋል፡፡

ፖሊስም በተለያዩ የፈረንሳይ ከተሞች የንብረት ውድመት የሚያደርሱ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስና በውሀ በመበተን ስራ ላይ ተጠምዷል፡፡

ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከተመረጡ ጀምሮ እንደዚህ የከፋ ተቃውሞ ገጥሟቸው አያውቅም እየተባለ ነው፡፡

ፕሬዝዳንቱ በቤተ መንግስታቸው ባለ ስልጣኖቻቸውን ሰብስበው በጉዳዩ ዙሪያ በስፋት መክረውበታል፡፡

ማክሮን ከካቢኔ አባሎቻቸው ጋር ከተመካከሩ በኋላ በሚቀጥለው ወር በነዳጅ ምርቶች ላይ ሊጥሉት የነበረውን ቀረጥ ለማዘግየት ተገደዋል፡፡

ፖሊስ እስካሁን በአመፁ ከተሳተፉት መካከል ቀንደኛ የተባሉትን 378 ሰዎች በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በዚህ ሳምንት ወደ ሰርቢያ ለሁለት ቀናት ሊያደርጉት የነበረውን ጉብኝት በቀውሱ ሳቢያ መሰረዛቸውም ተሰምቷል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *