loading
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ረዳት ተጠሪ ቲቦር ናግይ ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ፡፡

አርትስ 19/03/2011

ረዳት ተጠሪው በጉብኝታቸው ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ቆይታ እንደሚያደርጉ ተገልጿል፡፡ረዳትተጠሪው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ህዳር 29 በሚያደርጉት ቆይታ ጅቡቲ፣ ኤርትራ እና ኬንያን ይጎበኛሉ ተብሏል፡

በጉብኝታቸውም አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር በንግድ ፣ በሰላም እና ደህንነት ዙሪያ በጋራ በምትሰራባቸው ጉዳዮች ዙሪያከሀገራቱ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩም ነው የተገለጸው።

የአፍሪካ ህብረት በአዲስ አበባ በሚያካሂደው ከፍተኛ የምክክር መድረክ ላይም ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ዘገባው የፋና ነው

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *