loading
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አቶ አድጎ አምሳያን ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አቶ አድጎ አምሳያን ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ

አርትሰ ታህሳስ 19 2011

የቤጉህዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ትላንት ባካሄደው ስብሰባ አቶ አድጎ አምሳያን ሊቀመንበር አድርጎ የመረጠው የቀድሞው ሊቀመንበር አቶ አበራ ባየታ ያስገቡትን የመልቀቂያ ደብዳቤ ተቀብሎ ነው፡፡ማዕከላዊ ኮሚቴው የተጓደሉ ሶስት የስራ አስፈፃሚ አባላትን ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ወደ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴነት ከፍ አድርጓል።

አዲሱ ሊቀመንበር ለህዝብ እና ለድርጅቱ መርሆች ቅድሚያ እሰጣለሁ ብለዋል።

ከማዕከላዊ ኮሚቴው ጋር በመደጋገፍም እንችላለን ነው ያሉት፡፡

በፍላጎታቸው ሃላፊነታቸውን ለለቀቁት የቀድሞው የቤጉህዴፓ ሊቀመንበር አቶ አበራ ባዬታ አክብሮታቸውን ጠቅሰው የርሳቸው ድርጊት ለሌሎች አባላት በአርአያነት የሚጠቀስ እንደሆነ መናገራቸው ከኢዜአ ያገኘነው ተጨማሪ መረጃ ያመለክታል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *