loading
እጅን መታጠብ ለብቻው ከጤና መታወክ አይታደግም ተባለ

ምግብ ከመመገብ በፊትና በኋላ እጅን መታጠብ ቢለመድም ሙሉ ለሙሉ በሽታ የሚተላለፍበትን
መንገድ ለመቆጣጠር ግን አያስችልም አለ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር
በሚኒስቴሩ የሃይጅንና የአካባቢ ጤና አጠባበቅ ዳይሬክተር አቶ ዳኘው ታደሰ እንዳሉት እጅን በመታጠብ
ብቻ በሽታን መከላከል ስለማይቻል የግልና የአካባቢ ንፅህናን መጠበቅ አማራጭ የለውም ።
ህብረተሰቡ እጅ መታጠብን ልምድ እንዲያደርግ የተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ኢትዮጵያ ውስጥ
ውጤታማ ለውጥ እንዲታይ አድርጓል ያሉት ዳይሬክተሩ 32 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ግንዛቤውን
አዳብሮ ተግባራዊ ማድረግ እንደቻለም ተናግረዋል።
የተገኘው ውጤት ቀጣይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገባ ያሳያል ብለዋል ።
እንደዳይሬክተሩ የመቀንጨር ችግርን በ 2022 ከኢትዮጵያ ለማጠፋት ታልሞ በተጀመረው ተግባር
እጅን መታጠብ በሽታውን ለመቆጣጠር ወሳኝ ሚና እንዳለው ተደርሶበታል። በተለይ በአማራና
በትግራይ ክልሎች ተጨባጭ ለውጦች መታየታቸውንም ተናግረዋል።
የዘንድሮው የዓለም እጅ መታጠብ ቀን በመላው ኢትዮጵያ ጥቅምት 10 ቀን እንደሚከበር ሚኒስቴሩ
ይፋ አድርጓል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *