loading
በማህበራዊ ሚዲያ የሃሰት ዜናዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦችን የሚገራ ህግ እየተዘጋጀ ነው ተባለ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በመንግስት ዓመታዊ ዕቅድ ዙሪያ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ እንደተናገሩት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተከፍሏቸው የሃሰት ዜናዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦች መኖራቸውን መንግስት ደርሶበታል።

እነዚህ ግለሰቦች ህዝቡን በማደናገር ከተለያዩ አካላት ጥቅም የሚያገኙ እና የሚከፈላቸው ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ያልታወቁ ግለሰቦችን ሃሳብ ከመቀበል እንዲታቀቡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

አክለዉም እንዲህ ያሉ ግለሰቦችን ተጠያቂ ለማድረግ ህግ እያዘጋጀን ነው ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የመገናኛ ብዙሃን እና ባለሞያዎች ለውጡ እንዲቀጥል ለማድረግ ትልቅ ሃላፊነት አለባቸው ብለዋል።

የሚዲያ ነፃነትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡

በቂ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ሚዲያ ተቋማት ከመርህ እንዳይወጡ እና ወገንተኛ እንዳይሆኑ ስፖንሰሮችና የሚመለከታቸው ተቋማት እገዛ ሊያደርጉላቸው እንደሚገባም አሳስበዋል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *